www.maledatimes.com የፕሮፌሰር መስፍን እና የጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ግንኙነት እና የፖለቲካዊ ፋይዳ! - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Addis Admas  >  Current Article

የፕሮፌሰር መስፍን እና የጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ግንኙነት እና የፖለቲካዊ ፋይዳ!

By   /   July 22, 2018  /   Comments Off on የፕሮፌሰር መስፍን እና የጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ግንኙነት እና የፖለቲካዊ ፋይዳ!

    Print       Email
0 0
Read Time:49 Second

[ቴዲ ድንቅ – አትላንታ]

ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያምና ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን የሚያመሳስላቸው ብዙ ነገር አለ። ሁለቱም የሚያምኑበትን ነገር ፊት ለፊት ይናገራሉ። ሁለቱም ቀጥታ ወደ ነጥቡ ገብተው ያወራሉ እንጂ ዝባዝንኬ አያውቁም። ሁለቱም የሚናገሯቸው አርፍተ ነገሮች ለጥቅስ የሚበቁ ናቸው። ሁለቱም ፈጣሪን የሚፈሩ መንፈሳውያን ናቸው። ሁለቱም ብዙ የጭቃ ጅራፍ ወርዶባቸው በሰፊ ትከሻቸው ችለዋል። ሁለቱም ለእርቅና ለፍቅር ትልቅ ልብ አላቸው።

…… ሁለቱም ያለፈውን በደል ይቅር በማለት ያምናሉ። ሁለቱም በሰላማዊ ሽግግር እንጂ በጦርነትና በፍልጠው ቁረጠው አያምኑም። ሁለቱም ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ያለፉትን በማሰርና በመግደል ሳይሆን በይቅርታና በምህረት ሰላማዊ ሽግግር እንድታደርግ አጥብቀው ያምናሉ። ሁለቱም አከራካሪና ብዙ ውዝግብ ሊፈጥርባቸው እንደሚችል እያወቁም ቢሆን ያመኑበትን ነገር ከማድረግ ወደኋላ አይሉም። ሁለቱም ደፋሮች ናቸው። እነዚህ ሁለቱ የኢትዮጵያ ኩራት ናቸው።

ሁለቱም ለኔ ቀና ብዬ የማያቸው የሞራል ልዕልና ያላቸው ሰዎች ናቸው። ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም በህይወት እያሉ ዕድሜያቸውን ሙሉ ሲመኙት የነበረውን፣ ለሁላችንም ከሳቸው ቅርብ ለነበርን ሁሉ በየቀኑ “ኢትዮጵያ የሚያስፈልጋት የይቅርታና የምህረት፣ የፍቅርና የሰላም ጉዞ – የማንዴላ ዓይነት ሰው ነው” እያሉ ሲነገሩን የነበረውን በዓይናቸው ለማየት በመብቃታቸው ከሳቸው ባላነሰ ተደስቻለሁ።

ፖለቲካዊ ፋይዳቸው ሁሉንም በፍቅር መግደል እና በእውነተኛነት ጽናት ፣ትክክለኛውን ነገር በግልጽ መናገር ነው።

Image may contain: Henok Degfu, smiling
Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

♦ “ ትክክለኛ ፍትሕ አይሰጡም” የተባሉት የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛ ከችሎት እንዲነሱ ተጠየቀ !

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar