www.maledatimes.com በሃገራችን ላለው ችግር የሴቶች ተደራጅቶ መታገል አስፈላጊ እና ወቅታዊ ምላሽ ነው፦ - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

በሃገራችን ላለው ችግር የሴቶች ተደራጅቶ መታገል አስፈላጊ እና ወቅታዊ ምላሽ ነው፦

By   /   December 11, 2014  /   Comments Off on በሃገራችን ላለው ችግር የሴቶች ተደራጅቶ መታገል አስፈላጊ እና ወቅታዊ ምላሽ ነው፦

    Print       Email
0 0
Read Time:3 Minute, 0 Second

ቀን 10/12/2014

ኤደን መስፍን, ኖርዌይ

 

ዛሬ ዛሬ ከረጅም አመታት ጀምሮ በሃገራችን የተነሳው የሴቶች መብት ይከበር የሚለውን ይህዝብ ጥያቄ

ለመቃረን እስኪመስል ድረስ ከባለፉትም ጊዜያቶች በባሰ ሁኔታ የሴቶች መብት እየተጣሰ ይገኛል።

ከዛም አልፎ ተቆርቋሪ አካል የሌላቸው የሃገራችን ሴቶች ህይወታቸው አሳሳቢ ደረጃ ላይ ይገኛል።

ለዚህም በየጊዜው ወደ ተለያዩ አፍሪካና አረብ ሃገራት በተለይም በሱዳን በየመን የሚፈልሰው

የኢትዮጵያውያን ሴቶ ች ቁጥር መጨመር ማረጋገጫ ነው። በተለያዩ በሱዳን በየመንና በተለያዩ አረብ

ሃገራት ያሉ ሴቶች እህቶቻችን ተጠሪ እንደሌላቸው በመገመት የየሃገራቱ ዜጎች እና መንግስታት

እንደፈለጉ ሲያሰቃዩዋቸው እያየን ያለነው እውነታ ነው። ተጠሪ እንደሌላቸውም በቅርቡ በወያኔ ኤምባሲ

ፊለፊት ተደፍራ የተጣለችው እህታችን እና ወደዛው አካባቢ እየደረሰ ያለው ስቃይ እና የስርአቱ ምላሽ

ማረጋገጫ ናቸው። ሌላው መቼ ከእኛ ከ ኢትዮጵያውያን አዕምሮ የማይወጣው በቅርቡ በሳዑዲ አረቢያ

በእህቶቻችን የደረሰው ግፍ እና ብሄራዊ ውርደትን ተያይዞ መንግስታችሁ ነኝ ባዩ የሰጠው ምላሽ

የምትፈልገውን ለም መሬት ከኢትዮጵያ በመውሰድ በስርአቱ ተጠቃሚ የሆነችው ጎረቤት አገር ሱዳን

በኢትዮጵያውያን ሴቶች እየተፈጸመ ያለው በደል መቼም ቢሆን ከእኛ ሴቶች ብቻ ሳንሆን ኢትዮጵያዊ

ለሆነ ሁሉ የእግር እሳት እንደሆነ ነው። የእነዚህ ሃገራትህዝብ እና መንግስታት እንደፈለጉ መሆናቸው

የወያኔን ለቡድን እንጂ ለህዝብ ዴንታ ቢስነት መገንዘባቸው ይመስላል። ለነገሩ በውጭ ሃገራት አልን

እንጂ ኢትዮጵያውያን ሴቶች በ።ሃገራቸው የሚደርስባቸ መከራ እና እንግልት ከቀን ወደቀን እየተባባሰ

ነው።እንደውም የዚህ ስርአት ዋና ተጠቂ ሴቶች መሆናቸውን በመዲናችን አዲስ አበባ በገሃድ የሚታይ

ነው።አዲስ አበባ ዓለም ዓቀፍ ከተማ እንደመሆኗ እንግዶችን ሊስብ የሚችሉ በርካታ ሰራዎችን መስራት

እየተቻለ ለወገን ለሃገር እና ስለነገው የማያስበው ይህ ስርዓት ለዚሁተግባር ደላሎችን በማሰማራት እና

የተለያዩ ነገሮችንበመጠቀም ቆነጃጅት እህቶቻችንን ለተርካሻ ስራ እያሰማራ ይገኛል።ከዚህም ሌላ በዚሁ

ሃገር አጥፊ ስርአት ባመጣው ቅጥያጣ ሙስና መስፋፋት የአስተዳደር ብልሹነት እና ብቃት ማነስ የተነሳ

በተፈጠረው የኑሮ ውድነት ታዳጊ ሴቶች ሳይቀሩ ኑሮን ለማሸነፍ ስጋቸውን ሸጠው ለመኖር መገዳደቸው

በመዲናችን ጎዳና እየታየ ያለ ሃቅ ነው።ይህ ትውልድን ጎጂ ተግባርም በአሁኑ ወቅት ወደ ተለያዩ ሃይ

ስኩል እና ኤለመንተሪ ትምህርት ቤቶች አቅራቢያ እየተስፋፋ ይገኛል። በበርካታ የአዲስ አበባ ት/ቤቶች

አካባቢ የሺሻ የጫት እና የመጠጥ ቤቶች ንግድ ተጧጡፏል።የነዚህ ነገሮች በትምህርትቤቶች አካባቢ

መስፋፋት ደግሞ ታዳጊዎችን ወደ አላስፈላጊ መንገዶች መምራቱ የታወቀ ነው። ይህም ተጽእኖ በሴቶች

እህቶቻችን ላይ የሚያደርሰው ጉዳት መጠነ ሰፊ ነው። ለዚህም ጉዳይ ስርአቱ መደሰቱን ለወላጆች ጩከት

ዝም በማለት እና ስለጉዳዩ ሲነሳ ጆሮ ዳባልበስ በማለት አረጋግጦልናል። በቅርቡ በታዳጊዋ ሃና ኦላንጎ

ላይ የደረሰው ግፍ የተሞላበት ድርጊት የዚህ ማረጋገጫ ነው። እንደዚሁም ስርዓቱ ለሴቶች ምንም ትኩረት

እንዳልሰጠ በርእዩተ አለሙ፤ በማህሌት ፋንታሁንና ኤዶም ካሳዬ እንዲሁም በሌሎቹም ስርዓቱን

በመቃወማቸውና በብዕራቸው የስራአቱን እኩይ ሴራ ስላጋለጡ በእስር ቤት የሚደርስባቸው መከራ እና

እንግልት ማረጋገጫ ነው።

የሆነው ሆኖ ሃያሶስት ዓመት ያስቆጠረው የጥፋት ስርዓት አንድም ቀን ለሴቶች መብት ሲቆም አላየንም

አንድም ደረጃ የሴቶችን መብትሲያሻሽል አላየንም ያሻሽላል ብለንም አንጠብቅም።የነሰምሃር እና

መሳዮዎቹዋ እና የስርዓቱ ተጠቃሚዎች ቅምጥል ኑሮ እና እንክብካቤ የአብዛኛው የስርዓቱ ሰለባ እና

የችግሩ ገፈት ቀማሽ የሆነውን ሴቶች ኑሮና የመብት ደረጃ ሊወክል አይችልም። እንደውም ማስተዋል

ለቻለ ይህ ስርአት በቆየ ቁጥር አሁን ላይ በሃገራችን ሴቶች ላይ ያለው ጥቃት ምን ደረጃ ሊደርስ

እንደሚችል መገመት ይችላል።

ታዲያ የዚህ ስርአት ለጥፋት መነሳትን የተረዳን እና የጥፋቱ ሰለባ የሆንን ሴት ኢትዮጵያውያን ከያለንበት

ተሰባስበን ስለመፍትሄው ልንወያይበት የሚገባበት፤ እንዲሁም ተግባራዊ ምላሽ ለመስጠት የምንደራጅበት

ጊዜ አሁኑኑ መሆን አለበት። ለዚህም በመጀመሪያ አሁን በስልጣን ላይ ያለው ስርአት ፍጹም የህዝብ እና

የሃገር ጠላት መሆኑን ማወቅ እና ማረጋገጥ፤ መፍትሄውም ይህን አጥፊ ቡድን ከህዝባችን ጫንቃ ማውረድ

በሚለው ቁርጥ አቋም ላይ መስማማት ይኖርብናል። ጠላትችን ከሆነው አምባገነናዊ ስርአት ጋር

ለምናደርገው እልህ አስጨራሽ ትግል በድል እንወጣ ዘንድ የሴት የጀግኖቻችንን ትግል ታሪክ መመርመርና

ማወቅ ወሳኝ በመሆኑ ገድላቸውን በማውሳት ልንማማር ይገባልም እላለሁ። እንደነ እቴጌ ጣይቱ እና

ሌሎችንም ተጋድሎ በማስታወስ እኛም የነሱ አብራኮች መሆናችንን ባለመዘንጋት እንደነሱ ታሪክ መስራት

እንደምንችል በማመን ትግላችንን መጀመር ይኖርብናል። ስርአቱን ከማስወገድ ባሻገር በአገራችን

የተከሰቱት ያለፉት ታሪካዊ ስህተቶቻችንን እንዳይደገሙ ቆም ብለን እያሰብን ለወጠነው ዲሞክራሲያዊ

ስርአት እኛ ሴቶች ተደራጅቶ ለመታገል መነሳት አለብን። የኛ የትግል ተሳትፎ በአገራችን እየተቀጣጠለ

ባለው ህዝባዊ ትግል ላይ ሲደረብ የሚኖረው ሚና ቀላል አይደለም። ስለዚህ ስርዓቱ ከሃገራችን ተወግዶ

የህዝብ መብት ይከበር ዘንድ ህዝባዊ እና ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ትመሰረት ዘንድ እኛ ሴቶች

ተደራጅተን በመነሳት የበኩላችንን የትግል አሻራ እናበረክት ዘንድ ወገናዊ ጥሪየን አቀርባለሁ።

ህዝብ ያሸንፋል!!!

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 9 years ago on December 11, 2014
  • By:
  • Last Modified: December 11, 2014 @ 12:43 pm
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar