www.maledatimes.com በኢትዮጵያ ሕዝብ መራራ ትግል እብሪተኛው የወያኔ መንግስት መውደቁ አይቀርም!!ገዛኸኝ አበበ ከኖርዌ - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  AFRICA  >  Current Article

በኢትዮጵያ ሕዝብ መራራ ትግል እብሪተኛው የወያኔ መንግስት መውደቁ አይቀርም!!ገዛኸኝ አበበ ከኖርዌ

By   /   August 23, 2014  /   Comments Off on በኢትዮጵያ ሕዝብ መራራ ትግል እብሪተኛው የወያኔ መንግስት መውደቁ አይቀርም!!ገዛኸኝ አበበ ከኖርዌ

    Print       Email
0 0
Read Time:2 Minute, 3 Second

የኢአዲግ ወያኔ መንግስት የስልጣን ወንበር በትሩን በሀይል ከተቆናጠጠበት ጊዜ ጀምሮ የኢትዮጵያ ሕዝብ የአኖኖር ሁኔታ ከእለት ወደ እለት እያሽቆለቆለ እና እየወረደ በመምጣቱ ከምቼውም ጊዜ በበለጠ በአሁኑ ወቅት ሕዝቡ ኑሮን መቋቋም በማይችልበት አደገኛ ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኝ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የኑሮ ውድነት ተቋቁሞ መኖር ከባድ ፈተና እየሆነባቸው እንደሆነ የችግሩ ሰለባና ተጠቂ የሆኑት ሰዎች በየጊዜው ከሚያሰሙት ሮሮና ጩኸት መረዳት ይቻላል:: በአሁኑ ወቅት ጥቂትየስርአቱ ደጋፊዎች እና የወያኔ ካድሬዎች ካልሆኑ በስተቀር የኑሮ ውድነቱን መቋቋም በማይችሉበት ደረጃ ላይ ደርሰዋል:: በአሁኑ ሰአት መንግስት የሚያራምደው ፖሊሲ የመላው ኢትዮጵያን ሕዝቡ ፍላጎት እና ጥቅም ማዕከል ያላደረገ ሲሆን የተወሰኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን ብቻ ተጠቃሚ እያደረገ እንደሚገኝ ይታወቃል :: ሁሉን የኢትዮያ ህዝብ እና ክልል ተጠቃሚ ያላደረገው የመንግስት የልማት ስትራቲጂ ፖሊሲ እና በመላው ሀገሪቱ ላይ በስፋት ተንሰራፍቶ ያለው ሙሰኝነት ከእለት ወደ እለት የሕዝቡ የአኖኖር ሁኔታ እያሽቆለቆለ እና እየወረደ እንዲመጣ ካደረጉት ምክንያቶች ውስጥ ተጠቃሽ ሲሆኑ ለኑሮ ውድነቱ ግንባር ቀደም ተጠያቂው ሀገሪቱን እየመራው እና የሀገሪቱን ኢኮኖሚ እድገት በፍጥነት እያሳደጉኝ ነው የሚለው የወያኔ ኢህአዲግ መንግስት ነው:: ታስታውሱ እንደሆነ የወያኔ ቁንጮ የነበሩት ሞቹ የቀደሞ ጠቅላይ ሚኒስት መለስ ዜናዊ በአንድ ወቅት በአሥር አመት ዉስጥ «ኢትዮጵያ በምግብ እራሷን ትችላለች። እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በቀን ሶስቴ እንዲመገብ እናደርጋለን» ብለው ነበር ነገር ግን ይህ የአቶ መለስ ዜናዊ ንግግር የውሃ ላይ ሽታ ሆኖ ቀረ :: በአንጻሩአቶ መለስ የኢትዮጵያን ሕዝብ በቀን ሶስቴ እንዲመገብ እናደርገዋለን ያሉለት ኢህአዲግ ኢትዮጵያን በብቸኝነት በሀይል መግዛት ከጀመረ 23 አመት እየተጠጋ ሲሆነው በእነዚህ አመታቶች ውስጥ ምንም የተለወጠ ነገር የለም:: የወያኔ መንግስት በተቆጣጠረው በመገናኛ ብዙሃን እንደሚለፈልፉት የኢትዮጵያ ኢኮነሚው ዕድገቱ በፍጥነት ሽቅብ እየገሰገሰ ሳይሆን ወደታች እያሽቆለቆለ ይገኛል:: ኑሮ እጅግ መራራ ከመሆኑ የተነሳ የሰዉ የአኖኖር ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ በመድረሱ ዉስጥ ዉስጡን የሚያልቁት ወገኖቻችን ብዛት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ነዉ። በመላው አገሪቱ አዲስ አበባን ጨምሮ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ የመጣው የውሃ፣የመብራትና የቴሌኮም አገልግሎት ጥራት መጓደልና የአገልግሎት መቋረጥ እንዲሁም በአገሪቷ እጅግ ከፍተኛ የሆነ የዉጭ ምንዛሪ እጥረት እየታየ ሲሆን በኢኮኖሚ ችግር የተነሳ ሕዝቡ ያለውን የኑሮ ውድነት መቋቋም በማይችልበት ሁኔታ ውስጥ በመገገኘቱ በማንኛውም ጊዜና ሰሀት ግባታዊ ሕዝባዊ አመጽ ሊነሳና ትልቅ ችግር ሊፈጠር እንደሚችል የሚሰጉ ብዙዎች ናቸዉ።ደግሞሞ አይቀርም በአሁኑ ሰአት እንደሚታየው እና መረጃዎች እንደሚጠቁሙት የኢትዮጵያ ሕዝብ ለውጥን ይፈልጋል ህዝቡ ሀገሪቱን እየመራ ባለው የወያኔ መንግስት ለመመራት ፍቃደኛ አይደለም ከየቦታው የሚሰማው እና የሚታያው የሰበዓዊ መብት ረገጣው አፈናና ግድያው ቀጥሎ ባለበት ሁኔታ በየቀኑ እየተባባሰ የመጣው የኑሮው ውድነቱ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከወያኔ ኢህአዲግ መንግስት ጋር ሆድ እና ጀርባ ሆነው እንዲቀጥሉ እያደረጋቸው ነው::ከዚህም የተነሳ መንግስት በየቀበሌው፣በየመስሪያ ቤቱ የሚጠራቸው ሕዝባዊ ስብሰባ ላይ ለመገኛት ፍቃደኛ እና ደስተኛ እንዳይደለ ምንጮቻችን ይገልጻሉ:: ነገሮች በዚህ አይነት ሁኔታ ሊቀጥሉ አይችሉም:: የመረረው የኢትዮጵያ ሕዝብ መብቱን ለማስከበር ሆ ብሎ በወያኔ መንግስት ላይ መነሳቱና አንባገነኖችን ዳግም እንዳይነሱ ገርስሶ መጣሉ አይቀርም:: ስንቶቻችው በእኔ ሀሳብ ትስማማላችው:: ውድቀት ለአምባገነኑ የወያኔ መንግስት!!! ገዛኸኝ አበበ ነኝ ነሀሴ 17/2006

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

Traveler’s Alleged Crimes and Robbery at Bole Airport Raise Concerns

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar