www.maledatimes.com አምቦ ውጥረት ላይ ነች - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

አምቦ ውጥረት ላይ ነች

By   /   May 1, 2015  /   Comments Off on አምቦ ውጥረት ላይ ነች

    Print       Email
0 0
Read Time:57 Second

በአንቦ ዩኒቨርሲቲ የተፈጠረው ግርግር እና መንግስት የወሰደው ጥቃት አንደኛ አመትን አስመልክቶ የአንቦ ከተማ እና እና የዩኒቨርስቲው ተማሪዎች እንዲሁም የከተማው ነዋሪዎች በከፍተኛ ውጥረት ላይ ሲሆኑ ፣መንግስት በከተማዋ ያሰማራቸው የፌደራል ፖሊሶች እና የዩንቨርሲቲው ተማሪዎች ከፍተኛ ፍጥጫ ላይ ቢሆኑም ከዛሬ ነገ ብጥብጥ እና ችግር ይፈጠራል ተብሎ ተፈርⶆል ። ሆኖም ግን በዚሁ ጉዳይ በተነሳ የአንቦ ከተማ የውሃና መብራት እና የስልክ አገልግሎት ካገኘች ከ፩፪ ቀናት በላይ እንዳስቆጠረች በስፍራው ተዘዋውራ የነበረችው የማለዳ ታይምስ ዘጋቢ ወይዘሪት ኢትዮጵያ ገልጻለች።

ወይዘሪት ኢትዮጵያ ያናገረቻቸው አንዳንድ ሰዎች ሲገልጹም ለስራ ከአዲስ አበባ የመጡ የግብረ ሰናይ ድርጅቶችም አገልግሎታቸውን ሳይፈጽሙ ተመልሰው ወደ አዲስ አበባ በፍርሃት ምክንያት መመለሳቸው በጣም አሳሳቢ መሆኑን ጠቁመዋታል ። ሆኖም መንግስት ነጻነት ያልሰጠው ይሄው ህብረተሰብ በፍርሃት ድባብ ይዞት አፍኖት ያስቀመጠው ት0እግስቱ የፈነዳ እለት ችግሩ የተባባሰ ሊሆን ይችላል በማለት አስተያየቷን የማለዳ ታይምስ ዘጋቢዋ ጠቁማለች ።

ባለፈው አመት ቁጥራቸው በዛ ያለ የኦሮሞ ተወላጅ የሆኑ ኢትዮጵያውያኖች በመሞታቸው የመረረ ሃዘን የጠለቀባቸው እነዚሁ ተማሪዎች በዘር ጉዳይ እንደዚህ አይነት ችግር ውስጥ መዳረጋቸው እና ከትግራ ልጆች ጋር ጥርስ ለጥርስ መናከሳቸው የነገውን ታሪክ ሊያበላሽ እና ሊያቆሽሸው ይችላል ሆኖም ግን ይቅር መባባልን ለምደን ሰላም ማውረዱ ተገቢ ይሆናል በማለት አንድ አዛውንት የገለጹ ሲሆን ለዚህ ሁሉ በደል ተጠያቂው የኢትዮጵያ መንግስት እና በዩኒቨርሲቲው ስር ያሰማራቸው ደህንነት ተብለው የተሰየሙት ተማሪዎች እና መምህራን ናቸው ሲሉ ጠቅልለዋል ። ማለዳ ታይምስ ።

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 9 years ago on May 1, 2015
  • By:
  • Last Modified: May 1, 2015 @ 4:00 am
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar