www.maledatimes.com የኢትዮጵያ ብርቅዬ አትሌት እና የአሜሪካ የሰደት ህይወቷ - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

የኢትዮጵያ ብርቅዬ አትሌት እና የአሜሪካ የሰደት ህይወቷ

By   /   October 2, 2015  /   Comments Off on የኢትዮጵያ ብርቅዬ አትሌት እና የአሜሪካ የሰደት ህይወቷ

    Print       Email
0 0
Read Time:1 Minute, 45 Second

ኢትዮጵያዊቷ ብርቅዪ አትሌት እና አሳዛኙ የአሜሪካ ገጠመኟ
“ወደ ኢትዮጵያ ከምመለስ እራሴን እዚሁ ባጠፋ እመርጣለሁ”ሌላኛው አትሌት
የ18 አመቷ ገነት ሊሪ በ400 ሜትር ወድድር ብሄራዊ ሪኮርድ በመሰበር አገሪቱ ካፈራቻቸው እና ሰሟን ከሚያሰጠሯት ጥቂት ብርቅዮ አትሌቶች መካከል አንዷ ስትሆን በመጭው 2016 እኤአ ኢትዮጵያን በመወከል ወደ ብራዚል ትጓዛለች ተብላ ከፍተኛ ተሰፋ የተጣለባት አትሌት ነበረች።ይሁን እና ከወራት በፊት ወደ አሜሪካ ለውድድር ተጉዛ “በ አገሬ ኢትዮጵያ ውስጥ የፖሊቲካ አባል ካልሆንሺ በሚል ምክንያት የተለያዩ በድሎች ደረሰወብኛል” በማለት አዚያው አሜሪካ የቀረችው ብርቅየዋ አትሌት ገነት ኑሮ በአሜሪካ አልጋ በአልጋ አልሆንልሽ ብሏታል።
እንደ ሰሞነኛው ታዋቂው የዋሽንገተን ፖስት እና የአንግሊዙ ጋርዲያን ጋዜጣ ተመሳሳይ ዘገባዎች ከሆነ ከሰድሰት ወራት በፊት አሜሪካ ወስጥ የጥግኝነት ማመልከቻ አቅርባ አስካሁን ድረስ ምላሽ ያላገኘችው አትሌት ገነት የመጀመሪያዎቹ ሳምንታት ኑሮ በአሜሪካ እጅግ ፈተናዎች የተሞሎባት ነበር ። በወር 400 ዶላር የተከራየችውን ቤት ኪራይ መክፈል ባለመቻሏ ለተወሰኑ ቀናት ከ ደጃፍ አሰከ ማደር ደረሳለች።በአሁኑም ወቅት ቢሆን የምትጠጋው (የሚረዳት ባለመኖሩ) ጉዳይዋን ከያዘላት ግለሰብ አንሰተኛ ክፍል ወስጥ ከሶፋ ላይ በመተኛት ለመዳበል ተገደዳለች ። ምንም እንኳን አርሱዋን የመሰሉ ወደ 30 የሚጠጉ ኢትዮጵያዊይን አትሌቶች ዋሽንግተን ዲሰ አቅራቢያ ቢኖሩም የቤተሰብ ነገር ሲነሳ ገነት የቤተሰቦቿ ፎቶዎችን (ታሪኮቿን )በማየት ማንባት ይቀናታል። በዚህ ወጣ ውረድ ውስጥ ግን ገነት አንድ ትልቅ ህልም አላት አርሱም ለየተኛው አገር እንደ ሆነ በውል ባታውቀውም በኦሎምፒክ ውድድር ላይ በመወዳደረ የወርቅ ሜዳሊያ ለማጥለቅ እና ሰንደቃላማ ማውለብለብ ነው ።
አንደ አትሌት ገነት ሁሉ አርሱም የገዢው መንግሰት” የፓርቲ አባል ካልሆንክ” ተበሎ የተለያዩ በደሎች እንደደረሱበት የሚናገረው የ25 አመቱ የረጅም ረቀት ጀግናው አትሌት ሃይሌ መንገሻ በአሁኑ ወቅት ዋሽንግተን ዲሲ ውስጥ በአንድ የመጠጥ መሽጫ መደብር ውስጥ ተቅጥሮ ኑሮውን የሚገፋ ሲሆን “ምንም እንኳን ብዙ ቀናት ቢጨልምም ፣የወደፊቱ እድሌን በቁርጠኝነት ባላውቀውም ወደ ኢትዮጵያ ከምመለስ እራሴን እዚሁ ባጠፋ እመርጣለሁ።” በማለት ደረሰብኝ ካለው በደሉ የተነሳ ከፈጥረቱ አንስቶ ደጉን እና ክፉን ካየባት አናት አገሩ( ኢትዮጵያ) ለጊዜውም ቢሆን ጥላ ከለላ የሆነችው አሜሪካንን መርጧል።
በተለያዩ ጊዜያት ኢትዮጵያን በአለማቀፍ የአትሊቲክስ ወድድሮች ላይ የሚወክሉት ፡ የአውሮፓ፣ የአሜሪካ ፣ የቻይና የመሳሰሉት ጎዳናዎች ላይ አረንጓዴውን ፣ቢጫውን እና ቀዩ ሰንደቃላማችንን በማውለብለብ የሁሌም አምባሳደሮቻችን የሆኑት ብርቅየዎቹ አትሌቶቻችን በሰበበ ባሰባቡ በወጡበት በመቅረት ለተለያዩ ባእዳን አገሮች የመሮጣቸው ነገር ሁኔታውን በቅርብ ለሚከታተሉ በርካታ ወገኖች በእጅጉ ያሳዘናል፣እንደ አገርም እንደ ሕዝብም ያሳፍራል ። ችግሩን ችግራቸን አድርገን መፍትሔውን ን በጋራ ካለፈላለግን “ዛሬ ቁጭ ብለው የሰቀሉት ነገ ቆመው ለማውረድ ይከበዳል “እንዳይሆን ደጋግሞ ማሰቡ ትልቅ አዋቂነት ነው። እስቲ እኛም ለምን ብርቅዪ አትሌቶቻችን ይኮበለላሉ? ብለን እነጠይቅ።

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 9 years ago on October 2, 2015
  • By:
  • Last Modified: October 2, 2015 @ 8:41 am
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar