www.maledatimes.com የኢትዮጵያ የድርቅ ሁኔታ እየተባባሰ መጥቶአል፣ መንግስትም ችልተኝነትን አብዝቶአል - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

የኢትዮጵያ የድርቅ ሁኔታ እየተባባሰ መጥቶአል፣ መንግስትም ችልተኝነትን አብዝቶአል

By   /   September 24, 2015  /   Comments Off on የኢትዮጵያ የድርቅ ሁኔታ እየተባባሰ መጥቶአል፣ መንግስትም ችልተኝነትን አብዝቶአል

    Print       Email
0 0
Read Time:1 Minute, 16 Second

በሃገሪቱ እየተስፋፋ የመጣውን አረንጓዴው ድርቅ እየተባለ የሚጠራው ከፍተኛ ረሃብ በመላው ሃገሪቱ እየተስፋፋ የመጣ ሲሆን በአሁን ሰአት በሰሜኑ ክልል ምስራቅ እና ደቡቡን በከፊል ከማጥቃቱም በላይ ከፍተኛውን ህዝብ ወደ ስደት ሲዳርግ ብዙሃኑን ደግሞ በተለያዩ የሃገሪቱ ትልልቅ ከተሞች ለልመና እንዲሰደዱ አድርጎአል ። በተለይም የገበሪው የዚህ አመት የምርት ሁኔት ማሽቆልቆል እና መንግስት በገበሬው ህዝብ ላይ የሚያሳርፈው ጫና ከፍተኛ ከመሆኑም በላይ ፣ምርቱን ማምረት ያልቻለው እና ያሉትን የቀንድ ከብቶችንም ለመሸጥ ወደ ከተማ የሚያጓጉዘው ገበሬ በፖሊሶች እየተነጠቀ ለጨረታ ሲቀርብበት ገበሬውን ለረሃብ እና ለከፍተኛ ችግር እንዲሁም ቤተሰቡን በየሜዳው ትቶ እንዲሄድ እያእረገው ነው ሲሉ ከአዲስ አበባ የተሰራጨው ሪፖርት ያመለክታል ።

ባሳለፍነው ሁለት ወራት የመንግስት ኮሙኒኬሽን ምንስቴር የሆኑት አቶ ሬድዋን ሁሴን ገበሬው ክብቶቹን በወቅቱ ስላላጠጣ ነው ብለው በአደባባይ ዋሽተውት የነበረውን ዘገባ እንደገና መልስ ብለው እርዳታ ያሽናል ብለው የአለም መንግስታትን መማጸን የቻሉበት አጋጣሚ እንደነበር ቢታወስም የጉዳዩ ተያያዥነት የመጣው የኢትዮጵያ መንግስት ኦባማን እና ሌሎች የአፍሪካ መሪዎችን ለመቀበል ያቀረበውን በጀት እንዳይቆረጥበት ያዘጋጀው እቅድ ነሲሉ ይሄውም ከ8፣ሚሊዮን ኣሜሪካን ዶላር በላይ ለዚኢያ ስብሰባ የታቀደ አላማ ላይ እንዲውል ሃገሪቱ ለስብሰባው መበጀቷን ሪፖርቱ ያመለክታል ፤ ይህ በእንዲህ እንዳለ ፕረዚዳንት ኦባማ ለሶስት ቀን ጉብኝቱ ብቻ 2.4 ሚሊዮን ዶላር ብቻ የከፈለ ሲሆን ይህም ከሁለት መቶ አባል ሰራተኞቹ እና የአየር ሃይል አባላቶቹ ጭምር እና ፣የበረራ ቁጥጥር ክፍል የሚያደርጉትንም የሚጨምር እንደሆነ ገለጸዋ አብራርቶአል ሆኖም  ሌሎች የአፍሪካ መሪዎች ግን በአፍሪካ የኢኮኖሚ ደረጃ ብች ሊንቀሳቀሱ የሚችሉ ሲሆን ይህን ያህል ወጭ የሚሸፍኑ ኣልሆኑ ይታወቃል በዚህ ጉዳይ ላይ ሃገሪቱ ከትርፍ ይልቅ በኪሳራ ልትንቀሳቀስ ትችላለች የሚለው ከፍተኛ ግምት የተሰጠው ከመሆኑም በላይ መንግስት ለሃገሩ እና ለህዝቡ እንዲሁም  ለህልውናው ቸልተኛ በመሆኑ አስጊ ሁኔታ ላይ ነው ያለነው ሲሉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገልጸዋል።    እረሃቡን ለማየት ሊንኩን ይጫኑ   https://www.facebook.com/218987881627147/videos/414838942042039/

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 9 years ago on September 24, 2015
  • By:
  • Last Modified: September 24, 2015 @ 11:12 pm
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar