www.maledatimes.com የጋዜጠኛ ሙሉጌታ ሉሌ መልካም ስም ከመቃብር በላይ ዘላለማዊ ሆኖ ይኖራል ዘላለማዊ ሆኖ ይኖራል (ጋዜጣዊ መግለጫ) - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

የጋዜጠኛ ሙሉጌታ ሉሌ መልካም ስም ከመቃብር በላይ ዘላለማዊ ሆኖ ይኖራል ዘላለማዊ ሆኖ ይኖራል (ጋዜጣዊ መግለጫ)

By   /   October 6, 2015  /   Comments Off on የጋዜጠኛ ሙሉጌታ ሉሌ መልካም ስም ከመቃብር በላይ ዘላለማዊ ሆኖ ይኖራል ዘላለማዊ ሆኖ ይኖራል (ጋዜጣዊ መግለጫ)

    Print       Email
0 0
Read Time:39 Second

ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት እንዲረጋገጥ፤ ብሎም ለአዲሱ የፕሬስ ትውልድ ፈር ቀዳጅ የነበረው ጋዜጠኛ ሙሉጌታ ሉሌ ከዚህ አለም በሞት መለየቱ ለብዙዎች የኢትዮጵያ ነጻ-ፕሬስ ጋዜጠኞች እና ቤተሰቦች መሪር ሃዘን ነው። ጋዜጠኛ ሙሉጌታ ሉሌ በአንደበቱ እውነትን የመሰከረ፤ በሰላ ብዕሩ ሃቅን የፈነጠቀ ለኢትዮጵያ ጋዜጠኞች ምሳሌ ሆኖ ያለፈ ታላቅ ኢትዮጵያዊ ነው። ጋሽ ሙሉጌታ ሉሌ በህይወት በነበረበት ወቅት መልካም ነገርን ሰርቶ አልፏልና በመልካም ተግባሩ ይታወሳል። የኢትዮጵያ ታሪክ ሲነሳ፤ የነጻ-ፕሬስ ጋዜጠኞች ታሪክ ይወሳል። የነጻ-ፕሬስ ጋዜጠኞች ገድል ሲታወስ ደግሞ፤ የጋዜጠኛ ሙሉጌታ ሉሌ መልካም ስም እንደ ፈርጥ ያንጸባርቃል። በውጭ አገር የምንገኝ የኢትዮጵያ ነጻ-ፕሬስ ጋዜጠኞች፤ ጋሽ ሙሉጌታ ሉሌን እንደታላቅ ወንድም፤ እንደሙያ አጋር እና እንደ ጥሩ ምሳሌ እያነሱ መልካም ተጋድሎውን ያስታውሳሉ። መልካም ስም ከመቃብር በላይ ይውላልና የጋሽ ሙሉጌታ ስራ እና ስም ለዘለአለም በክብር ይታወሳሉ። አምላክ ነፍሱን ይማር። በውጭ አገር የሚገኙ የኢትዮጵያ ነጻ-ፕሬስ ጋዜጠኞች

Mulugeta Lule 2 (1)

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 9 years ago on October 6, 2015
  • By:
  • Last Modified: October 6, 2015 @ 9:17 pm
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar