www.maledatimes.com የጽዮንን በዓል አክብረው ከተመለሱ ምዕመናን ውስጥ መኪና ተገልብጦ የአራት ሰዎች ሕይወት አለፈ - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

የጽዮንን በዓል አክብረው ከተመለሱ ምዕመናን ውስጥ መኪና ተገልብጦ የአራት ሰዎች ሕይወት አለፈ

By   /   December 2, 2014  /   Comments Off on የጽዮንን በዓል አክብረው ከተመለሱ ምዕመናን ውስጥ መኪና ተገልብጦ የአራት ሰዎች ሕይወት አለፈ

    Print       Email
0 0
Read Time:44 Second

ከዘመድኩን በቀለ በየዓመቱ ህዳር 21 ቀን በታላቅ መንፈሳዊ ሥነሥርዓት የሚከበረውን የህዳር ጽዮን በዓል ለማክበር ከአዲስ አበባ ተነስቶ የነበረው የአቡነ አሮን መንፈሳዊ የጉዞ ማኅበር መኪና 60 ተጓዥ ምእመናንን ይዞ ከበዓሉ መልስ ዛሬ ከወልድባ ሰቋር ጉብኝት በኋላ ወደ ጎንደር በመመለስ ላይ ሳለ ከአንባ ጊዮርጊስ ወጣ ብሎ ልዩስሙ 44 ተብሎ ከሚጠራው ሥፍራ ላይ አደጋ ደርሶበት ብዙ ሰው ተጎዳ ። axum በአደጋው እስካሁን 3 ተጓዥ መንገደኞች ሕይወታቸውን ያጡ ሲሆን ቁጥራቸው በዛ የሚሉት ደግሞ ቀላልና ከባድ የሆነ ጉዳት ደርሶባቸው በጎንደር ሆስፒታል በሕክምና ላይ ይገኛሉ ። ከእነዚህ መንገደኞች መሃል በተለይ ዘማሪ ምትኩ በከባድ ጉዳት ውስጥ እንደሚገኝ በአደጋው ሰዓት ወዲያው በመድረስ የሞቱትንም ሆነ የቆሰሉትን ወደ ሆስፒታል የወሰደው የማኀበረ ወይንዬው ሰብሳቢ መ/ር ደረጀ ነጋሽ በስልክ ገልጾልኛል ። የአደጋው አድራሽ በቅጽል ሰሙ ቀይ ሽብር በመባል የሚታወቀው የቻይና ስሪት የሆነው መኪና ሲሆን የአደጋውን መንስኤ ግን የክልሉ ፖሊስ እያጣራ መሆኑንም ደረጀ አክሎ ነግሮኛል ። አሁን ይህን ማስታወሻ በመጻፍ ላይ ሳለሁ ደረጀ የሟቾች ቁጥር ወደ 4 ከፍ ብሏል ብሎኛል።  ያረፉትን ነፍሳቸውን ይማር ።

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 9 years ago on December 2, 2014
  • By:
  • Last Modified: December 2, 2014 @ 1:32 pm
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar