Read Time:35 Second
(ዘ-ሐበሻ) ኢትዮጵያ የሚገኘው እና አሜሪካ በሚገኘው ቅዱስ ሲኖዶስ መካከል የተጀመረው እርቀ ሰላም ታላቅ ውሳኔ አስተላለፈ::
በአዲስ አበባው እና በውጭ ሃገር ያለው ሲኖዶስ ከብዙ ልፋት እና ሽምግልና በኋላ እርቀሰላሙ ተፈጽሟል:: በዚህም መሰረት በውጭ ሃገር ያለው ሲኖዶስ እና በሃገር ቤት ያለው ሲኖዶስ አንድ እንዲሆኑ ተወስኗል:: በዚህም መሰረት ፓትርያሪክ አቡነ መርቆሪዮስ ወደ መንበራቸው የሚመለሱ እንዲመለሱ ከስምምነት ተደርሷል::
አቡነ ማቲያስም እንዲሁ የቢሮ ሥራዎችን እንዲያከናውኑና በፕትርክናቸው የሚቀጥሉ ሲሆን ዋናው መንበር ላይ አቡነ መርቆሪዮስ እንዲቀመጡ መወሰኑንና እርቀሰላሙም በዚሁ መንገድ መጠናቀቁን የዘ-ሐበሻ ምንጮች ገልጸዋል::
እንደ ምንጮቻችን ገለጻ ከኢትዮጵያ የመጡት አባቶችም ሆኑ በውጭ ያሉት አባቶች ስብሰባ በሌሎች ጉዳዮች ላይ ይቀጥላል:: የፊታችን ቅዳሜ ከጠዋቱ በ10 ሰዓት ላይም ዶ/ር አብይ አህመድ ፓትርያርክ አቡነ መርቆርዮስን እና ሌሎች አባቶችን በዋሽንግተን ዲሲ እንደሚያነጋግሩ የዘ-ሐበሻ ምንጮች ጠቁመዋል::
Wondering where the comments are? We encourage you to use the share buttons below and start the conversation on your own!
- Click to email a link to a friend (Opens in new window) Email
- Click to share on Facebook (Opens in new window) Facebook
- Click to share on X (Opens in new window) X
- Click to share on LinkedIn (Opens in new window) LinkedIn
- Click to share on Pinterest (Opens in new window) Pinterest
- Click to share on Tumblr (Opens in new window) Tumblr
- Click to print (Opens in new window) Print



Print
Email
Average Rating