www.maledatimes.com የኢትዮጵያ ባለ ሙሉ ስልጣን አምባሳደር አቶ ፍጹም አረጋ እና ሌሎች የቆንጽላ ባለሟሎች በችካጎ የኢትዮጵያ ኮሙኒቲ ጋር ከፍተኛ ስብሰባ አካሄዱ ። - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  AFRICA  >  Current Article

የኢትዮጵያ ባለ ሙሉ ስልጣን አምባሳደር አቶ ፍጹም አረጋ እና ሌሎች የቆንጽላ ባለሟሎች በችካጎ የኢትዮጵያ ኮሙኒቲ ጋር ከፍተኛ ስብሰባ አካሄዱ ።

By   /   October 6, 2019  /   Comments Off on የኢትዮጵያ ባለ ሙሉ ስልጣን አምባሳደር አቶ ፍጹም አረጋ እና ሌሎች የቆንጽላ ባለሟሎች በችካጎ የኢትዮጵያ ኮሙኒቲ ጋር ከፍተኛ ስብሰባ አካሄዱ ።

    Print       Email
0 0
Read Time:1 Minute, 12 Second

Ambassador Fitsumwith maleda times Editor ad other community members

አምባሳደር ፍጹም አረጋ፣ የካሊፎርኒያው ቆንሱሌት ቢሮ አምባሳደር ብርሃነ መስቀል አበበ ሰኝ እና የሚንሶታ ቆንሱሌት ቢሮ  አምባሳደር እውነቱ በመሆን ወደ በሚድ ዌስት አካባቢ በችካጎ ከተማ አቅንተው ከማህበረሰቡ እና ከህዝቡ ጋር ግንኙነት በማድረግ አስፈላጊውን ስየስራ ክፍፍል ለመግለጽ እና ወደፊት መንግስት ከህዝቡ ጋር እንዴት መገናኘት አለበት የሚለውን ለመግለጽ ባደረጉት ልዩ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከዚህ እለት ጀምሮ የኢትዮጵያ ኮሙኒቲ አሶሴሽን ኦፍ ሽካጎ ኤምባሲውን በመወከል አስፈላጊዎችን ስራዎች መስራት እንደሚችል ተጠቁሟል ፣ ማናቸውንም በመንግስት በኩል ሊደረጉ የሚገባ ነገሮች ፣ ህዝቡ ወደ ሃገር ቤት መግባትም ፣ ሆነ መስራት፣ ልማት ላይ መሳተፍ የሚችለው በቅርበት ከሚገኘው ኮሙኒቲ ጋር በመገናኘት አብረን በመስራት በጋራ ሃገራችንን ይዘን መጓዝ አለብን ሲሉ ተደምጠዋል። በሚቀጥለው ኦክቶበር አስራ ሁለት በዴ ሞኒስ አይዋ ካፒታል ሜድዌስተርን ስቴት 601 ግራንድ አቬኑ የስብሰባ አዳራሽ አይዋ  ካሉ ህዝቦች ጋር ካሉ ኢትዮጵያኖች ጋር ውይይት እንደሚያደርጉ አምባሳደር ፍጹም ለማለዳ ታይምስ ተናግረዋል። አምባሳደር ፍጹም በመቀጠል በአባይ ጉዳይ ላይ በትላንትናው እለት የተነሳውን የግብጽን መግለጫ አስመልክቶ የማለዳ ታይምስ መረጃ ማእከል ባነሳው ጥያቄ ላይ ምላሽ ሰጥተውበታል፣ የአሜሪካ መንግስት የሰጠውን መግለጫ ብቻ በቂ ነው ፣ኢትዮጵያ በእኩል የሶስቱ ሃገራት ማለትም ሱዳን ግብጽ እና ኢትዮጵያ የአባይን ሪሶርስ መጠቀም አለባቸው ብለዋል። ቆንጽላ ብርሃነ መስቀል በበኩላቸው ኢትዮጵያ ለአርባ አመታት ስትራብ እንጂ ግብጽ ስትራብ አልታየም ይህም በውስጥ የነበረው የፖለቲካ ችግር ነው ሲሉ ተናግረዋል ። ሙሉውን ያድምጡት ።

የሚድዌስት አካባቢ ያሉ ማህበረሰባቶች ግልጋሎት
ሊሰጣቸው የሚችለው በሚንሶታ በሚገኘው የኮኑሌት ጀነራል ኦፊስ በአምባሳደር እውነቱ አማካይነት እንደሆነ የገለጹት አምባሳደር እውነቱ
፣ ከኮሙኒቲው ጋር በቅርበት የምንሰራው ቀድሞውኑም ኮሚኒቲው ከአካባቢው ከህዝብ ጋር ስለሚሰራ እኛ ከእነሱ ጋር መስራታችን ተደራሽነታችን
የላቀ ነው ብለው ተናግረዋል።  

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

Traveler’s Alleged Crimes and Robbery at Bole Airport Raise Concerns

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar