www.maledatimes.com አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሁሉም ካምፓሶች የፊት ጭንብል መልበስ ግዴታ መሆኑን አስታወቀ - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Addis Admas  >  Current Article

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሁሉም ካምፓሶች የፊት ጭንብል መልበስ ግዴታ መሆኑን አስታወቀ

By   /   May 25, 2020  /   Comments Off on አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሁሉም ካምፓሶች የፊት ጭንብል መልበስ ግዴታ መሆኑን አስታወቀ

    Print       Email
0 0
Read Time:40 Second

**************No photo description available.
በአገራችን የሚታየው የኮሮናቫይረስ ስርጭት ከዕለት ወደ ዕለት እያደገ በመምጣት በአሁኑ ወቅት አሳሳቢ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ የገለጸው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከግንቦት 17 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ በሁሉም ካምፓሶቹ የፊት ጭንብል ማድረግን አስገዳጅ የሚያደርግ መመሪያ አውጥቷል።

ዩኒቨርሲቲው የኮሮናቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል ቀደም ሲል ያስተላለፋቸው መሠረታዊ የመከላከል ዘዴዎች የሆኑት እጅ መታጠብ፣ ርቀት መጠበቅ እና የፊት ጭንብል መጠቀም በመላው የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ ዘንድ ተግባራዊ እንዲሆን በማድረግ የሚያበረታታ እንቅስቃሴ ሲያደርግ መቆዩቱን አስታውሷል።

ነገር ግን የተላለፉት የጥንቃቄ እርምጃ መመሪዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ መላላት እየታየባቸው በመሆኑ እና የቫይረሱ ስርጭት እየተጠናከረ መምጣቱን ጠቅሷል።

ይህንን ተከትሎ ከግንቦት 17 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ማንኛውም ሰው የፊት ጭንብል ሳያደርግ ወደ ግቢ መግባት፣ በግቢ ውስጥ ያለ ጭንብል መንቀሳቀስ እና ጭንብል ሳያደርጉ በቢሮ ውስጥ ሥራ መሥራት በጥብቅ የተከለከለ መሆኑን አስታውቋል።

የዩኒቨርሲቲው ስታንዳርድስ ሴፍቲ እና ሴኪዩሪቲ ዳይሬክተር እና የሚመለከታቸው የሥራ ክፍል ሐላፊዎች መመሪያውን ተግባራዊ እንዲያደርጉም አሳስቧል።

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

Traveler’s Alleged Crimes and Robbery at Bole Airport Raise Concerns

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar