www.maledatimes.com የአውሮፓ ህብረት ኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ በህዳሴው ግድብ ለሚያደርጉት ድርድር ስኬታማነት ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታወቀ - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Addis Admas  >  Current Article

የአውሮፓ ህብረት ኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ በህዳሴው ግድብ ለሚያደርጉት ድርድር ስኬታማነት ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታወቀ

By   /   July 19, 2020  /   Comments Off on የአውሮፓ ህብረት ኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ በህዳሴው ግድብ ለሚያደርጉት ድርድር ስኬታማነት ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታወቀ

    Print       Email
0 0
Read Time:30 Second

የአውሮፓ ህብረት ኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ በታላቁ የህዳሴ ግድብ ዙሪያ ለሚያደርጉት ድርድር ስኬታማነት ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታወቀ፡፡
በአውሮፓ ህብረት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲና የደህንነት ክፍል ተወካይ እንዲሁም የህብረቱ ምክትል ፕሬዚዳንት ጆሴፕ ቦሬል በህዳሴው ግድብ ዙሪያ መግለጫ አውጥተዋል፡፡
በመግለጫቸውም ሶስቱ ሃገራት ከህዳሴው ግድብ ጋር በተያያዘ እያደረጉት ላለው ድርድር ስኬታማነት ህብረቱ ድጋፉን ያደርጋል ብለዋል፡፡
ከዚህ ባለፈም ሃገራቱ የጋራ መግባባት ላይ ለመድረስ ሊሰሩ ይገባልም ነው ያሉት፡፡
ሃገራቱ ይህን ካደረጉም ህብረቱ እገዛ እንደሚያደርግና ይህም መተማመንን በመፍጠር ውጥረትን ለማርገብ እንደሚረዳም አውስተዋል፡፡
ከዚህ ባለፈም የተፋሰሱ ሃገራት በኢንቨስትመንትና በውሃ ደህንነት ያላቸውን ግንኙነት ለማደስ እንደሚረዳቸውም አስታውቀዋል፡፡
ህብረቱም ደቡብ አፍሪካ በአሸማጋይነት ሶስቱ ሃገራት መግባባት ላይ እንዲደርሱ የምታደርገውን ጥረት እንደሚያበረታታም ገልጸዋል፡፡

 

 

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

Traveler’s Alleged Crimes and Robbery at Bole Airport Raise Concerns

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar