www.maledatimes.com ”ህወሓት በአባላቶቼ ላይ ለሚያደርሰው ግፍና ጭቆና መፍትሄ ይሰጠኝ” ሲል የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ት-ዴ-ፓ) ጠየቀ። - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Addis Admas  >  Current Article

”ህወሓት በአባላቶቼ ላይ ለሚያደርሰው ግፍና ጭቆና መፍትሄ ይሰጠኝ” ሲል የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ት-ዴ-ፓ) ጠየቀ።

By   /   July 19, 2020  /   Comments Off on ”ህወሓት በአባላቶቼ ላይ ለሚያደርሰው ግፍና ጭቆና መፍትሄ ይሰጠኝ” ሲል የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ት-ዴ-ፓ) ጠየቀ።

    Print       Email
0 0
Read Time:45 Second

 

ፓርቲው አቤቱታውን ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት፣ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ እንዲሁም ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በደብዳቤ ማሳወቁን ጠቁሟል።

የፓርቲው ሊቀ-መንበር ዶክተር አረጋዊ በርሄ ፓርቲው መሰረቱን ትግራይ ክልል በማድረግ ለኢትዮጵያ ህዝቦች ነጻነት፣ እኩልነትና ብልጽግና የሚታገል ነው ሲሉ ገልጸዋል።

ለዚህም አባላቶቹን በመመልመልና በማብቃት በትግራይ ክልል የተለያዩ እንቅስቃሴዎች እንደሚያደርግ አስታውቀዋል።

ይሁንና አባሎቻቸው ላይ በተደጋጋሚ ችግር እየደረሰ መሆኑንና የሚደርሰውን እንግልት ለሚመለከተው አካል በተደጋጋሚ በቃልና በጽሁፍ ማሳወቃቸውን አመልክተዋል።

በተለያዩ የትግራይ ክልሎች የሚገኙ የፓርቲው አባላት ከህግ አግባብ ውጪ ታስረው እየተሰቃዩ ነው ሲሉም ተናግረዋል ሊቀመንበሩ።

ለአብነትም በሽሬ ከተማ በፌስቡክ ጽፋችኋል ተብለው 128 ወጣቶች የታሰሩ ሲሆን በመቀሌ፣ በእንዳስላሴ፣ በዓዲግራት፣ አድዋ፣ እንትጮ፣ ኮረም፣ ወጀራት፣ ዓዲጉደም፣ ቆራሪት፣ ማይሃንሰ፣ ሁመራ፣ሽራሮ፣ ባድመና ሌሎችም ከተሞች የፓርቲው ደጋፊዎች ናችሁ በሚል ታስረው እየተሰቃዩ ነው ብለዋል።

 

ፓርቲው ለኢዜአ በላከው መግለጫ “ህወሃት በትግራይ ህዝብ፣ በትዴፓና በሌሎችም ሰላማዊ ፓርቲዎች ላይ የአገሪቱን ህገ-መንግስትና ሌሎችንም ህጎች በመጣስ የሰብዓዊ መብት ጥሰትና ጭቆና እያደረሰ በመሆኑ የፌዴራል መንግስት መፍትሄ ይስጠኝ” ሲል ጠይቋል።

 

 

 

 

 

 

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

Traveler’s Alleged Crimes and Robbery at Bole Airport Raise Concerns

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar