www.maledatimes.com የ4 ሰዎችን ህይወት በውሃ ሙላት ተቀጠፈ ! - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Addis Admas  >  Current Article

የ4 ሰዎችን ህይወት በውሃ ሙላት ተቀጠፈ !

By   /   August 28, 2020  /   Comments Off on የ4 ሰዎችን ህይወት በውሃ ሙላት ተቀጠፈ !

    Print       Email
0 0
Read Time:30 Second

የኦሞ ወንዝ ሞልቶ ዉኃ ከከባቸዉ መንደሮች ለማምለጥ የሞከሩ አራት የደቡብ ክልል ፤ የዳሰነች ወረዳ ነዋሪዎች ሞቱ።

የአካባቢዉ ባለስልጣናት ለጀርመን ድምፅ ሬድዮ ጣቢያ እንዳሳወቁት አራቱ ሰዎች በዉኃ የተበሉት ዉኃ ከከበባት ቶል-ታሌ ቀበሌ ወደ ደረቅ መሬት በጀልባ ለመሻገር ሲሞክሩ ጀልባቸዉ ተገልብጣ ነዉ።
ከሟቾቹ ሁለቱ እናት እና ልጅ ሁለቱ ደግሞ አዛዉንቶች ነበሩ።
በውኃ ተከበው የነበሩ ሌሎች 200 ነዋሪዎች ግን ከክልሉ በተላኩ ጀልባዎች ርዳታ ሙሉ በሙሉ ወደ ደረቅ አካባቢ መሻገራቸዉን ተሰምቷል።
የኦሞ ወንዝ ሙላት ከዳሳች ወረዳ አርባ (40) ቀበሌዎች መካከል 28ቱን አጥለቅልቋል። ከ15 ሺሕ በላይ ሰዎችን ከቤት ንብረታቸዉ አፈናቅሏል።
የዉኃ ሙላቱ ከ30 ዓመት ወዲሕ ከፍተኛ ጉዳት ሲያደርስ ያሁኑ የመጀመሪያዉ መሆኑን የጀርመን ድምፅ ሬድዮ ጣቢያ ዘግቧል። 
Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

Traveler’s Alleged Crimes and Robbery at Bole Airport Raise Concerns

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar