www.maledatimes.com የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ግብረሃይል ትጥቅ ለማስፈታት ትዕዛዝ የመስጠት ስልጣን አለው - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Addis Admas  >  Current Article

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ግብረሃይል ትጥቅ ለማስፈታት ትዕዛዝ የመስጠት ስልጣን አለው

By   /   November 5, 2020  /   Comments Off on የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ግብረሃይል ትጥቅ ለማስፈታት ትዕዛዝ የመስጠት ስልጣን አለው

    Print       Email
0 0
Read Time:53 Second

ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ በትግራይ ክልል የታወጀውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የሚያስፈጽመውና የሚያስተገብረው ግብረሃይል፣ ፖሊስ ወይንም ሌላ ማንኛውንም የጸጥታ ኃይል ትጥቅ እንዲፈታ የማዘዝ ስልጣን እንደተሰጠው ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ አስታወቀ። ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ዛሬ በተወካዮች ምክር ቤት በጸደቀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አተገባበርና የአፈጻጸም ወሰን ላይ ለጋዜጠኞች ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸው አዋጁ የሚጸናበትን ጊዜ፣ የአፈጻጸም ወሰንና አዋጁን በሚያስተገብረውና በሚያስፈጽመው ግብረሃይል ስልጣንና ተግባር ላይ ገለጻ አድርገዋል። አዋጁን የማስፈጸምና የማስተግበር ስልጣን የተሰጠው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ግብረሃይል መሆኑንም ተናግረዋል። የግብረሃይሉ ሰብሳቢ የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም መሆኑን ጠቁመው “ግብረሃይሉም ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ወይንም ለጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ይሆናል” ብለዋል። የአዋጁ የአፈጻጸም ወሰን በዋናነት በትግራይ ክልል ሲሆን እንደ አስፈላጊነቱ ግብረሃይሉ ሊያሰፋውና ሊያጠበው እንደሚችልም ዶክተር ጌዲዮን አመልክተዋል። “ግብረሃይሉ አዋጁ ተፈጻሚ በሚሆንበት ክልል ውስጥ ፖሊስ ወይንም ሌላ ማንኛውም የጸጥታ ኃይል ትጥቁን እንዲፈታ ትዕዛዝ መስጠት ይችላል” ብለዋል። አካባቢውን ለመቆጣጠርና ሰላምን ለማስፈን አስፈላጊውን እርምጃ የመውሰድ ስልጣንም ተሰጥቶታል ነው ያሉት። ግብረሃይሉ አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው ማንኛውንም የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ወደ ትግራይ ክልል እንዳይገባም ሆነ እንዳይወጣ ትዕዛዝ መስጠት እንደሚችል ዶክተር ጌዲዮን ገልጸዋል። ከእዚህ በተጨማሪ ግብረሃይሉ ሰዓት እላፊ ገደብ ለመጣልና የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስን መከልክል እንዲችል ስልጣን እንደተሰጠውም ማመልከታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

About Post Author

Abby

Internet reporter, freelancer and webmaster.
Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email

About the author

Internet reporter, freelancer and webmaster.

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

Traveler’s Alleged Crimes and Robbery at Bole Airport Raise Concerns

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar