www.maledatimes.com ሞረድ ሲደንዝ በቢለዋ ይሳላል - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

ሞረድ ሲደንዝ በቢለዋ ይሳላል

By   /   September 8, 2014  /   Comments Off on ሞረድ ሲደንዝ በቢለዋ ይሳላል

    Print       Email
0 0
Read Time:10 Minute, 50 Second

ሞረድ ሲደንዝ በቢለዋ ይሳላል

(የበዓሉ ግርማ ጉዳይ)

– ሲራክ ዮፍታሄ

 

ዛሬ የምንገኝበት ዲሞክራሲያዊና ቴክኖሎጂካዊ ዘመን ህዝባዊና መንግስታዊ እውቅና ስለነበረው አንድ ሰው የኦሟሟት ምስጢር ጥያቄ ማቅረብ ወንጀል አይደለም። ግርድፍ ማስረጃን አንተርሶ እውነታው እንዲታወቅ መጻፍም አስተዋይ ህሊና ላለው ሰው መጥፎነቱ አይታየውም። ይልቁንም ተጠየቅነቱ ፋይዳ የሚኖረው ለምን የአንድ ሰው አሟሟት ብቻ የሌሎች ወገኖቻችን አሟሟትም ይታወቅ የሚል መሰረታዊ ጥያቄ ከተነሳ ብቻ ነው። ይህም ቢሆን ይቻላል፡፡ እኔ ግን ጥያቄውን ያቀረብኩት በቅርብ ስለማውቀውና ካገኘሁት ማስረጃም ተነስቼ ነው። ሌሎቹ ደግሞ እንውቃለንና ማስረጃም አለን ብለው ቢነሱ መሰረተ ሀሳባቸውን ደጋፊ እንጅ ተቃዋሚ አይደለሁም ቢሉ አጠቃላይ ትኩረቱ ወደ ዋናው የኣቶ በዓሉ ግርማ አሟሟት ተጠየቅነት ያንደረድረናል።

 

ለዚህ ጽሑፌ መነሻ ምክንያት የሆነኝ የደራሲ በዓሉ ግርማን አሟሟት አስመልክተው ጋዜጠኛና ደራሲ አበራ ለማ ባቀረቡት ጽሑፍ ላይ እየቀረበ ያለው መረን የለቀቀ ስድብና ዉርጅብኝ አስገርሞኝ ነው። በተለይም አቶ ታሪኩ አባዳማ እና አቶ ተስፋዬ ተሰማ በECADF, በኣቡጊዳና ባንዳንድ ድረ ገጾች ላይ የአበራ ለማ ጽሑፍን በመቃወም ጽፈዋል። እንደ ግለሰብ መብታችውን አከብራለሁ። እንደየወል ጉዳይ ደግሞ ተቃውሟቸው ዘለፋና ሰብዕና ተኮር በመሆኑ የኣስተማሪነት መልእክት ስለሌለው እቃወማቸዋለሁ።

 

ደራሲ አበራ ለማ ከልጅነት እስክ ሽበት በሚታወቁበትና በሚጠሩበት በራሳቸው ስም መጻፋችው እራሱ፣ በራሳቸው የሚተማመኑና ጽሑፋቸውን ኣስመልክቶም ለሚነሳ ማናችውም ተችት ወይም ክስ ራሳችውን ችለው ለመጋፈጥ ዝግጁ መሆናቸውን ከወዲሁ ያሳያል። በአበራ ጽሑፍ ውስጥ ስማቸው የተጠቀሱ ግለሰቦችም እንዲሁ ራሳቸውን ችለው ለመከራከርም ሆነ ለመወያየት ከበቂ በላይ ብቃት ያላችውና ከራሳቸው አልፈው ለሌላው ሊቆሙ እንደሚችሉ ይታወቃል። ታድያ እኛ አንባቢያን ከግራና ከቀኙ የሚወረወሩትን መሰረታዊ ነጥቦች መርምረንና መዝነን ወደ አንድ ብይን ለመምጣት ከመሻት ይልቅ ቀድመንና አንድ ወገንን ደግፈን በስድብ ናዳ መረባረብ ” የምጣዱ እያለ የእንቅቡ ተንጣጣ ” አይሆንብንም? እዚህ ላይ ሩቅ ሳንሄድ አንተስ ለአበራ ጉዳይ ምን አገባህ ? የሚል ጥያቄ ቢቀርብ መልሴ አጭርና ግልጽ ነው። ይህም የታሪኩ አባዳማ እና የተስፋዬ ተሰማ ምክንያታዊ ያልሆነ ወገንተኝነትና አፈቀላጤነት ነው የሚል ይሆናል። የነእገሌን ስም ለምን ጠቀስክ ብሎ መጠየቅ አግባብነት አለው ቢባል እንኩዋን አንዱን ወገን በመዝለፍና አላግባብ በመፈረጅ የሚቀርብ ገጸ በረከት ግን ውሻ በበላበት ይጮሃል የሚል ትችት ማስነሳቱ አይቀርም። ወጣም ወረደ በአበራ ለማ ጽሑፍ ላይ የተሰጡትን አስተያየቶች አንተርሼ ግላዊ አስተያየቴን አንደሚከተለው አቀርባለሁ።

 

     ሀ. የአቶ ታሪኩ አባዳማ አስተያየትና ግላዊ ምልከታዬ

 

*** አቶ ታሪኩ ጋዜጠኛ አበራ ባቀረቡት ጽሑፍ ላይ ሁለት የተለያዩ ክፍሎች ኣስተያየት እንደሰጡና ሁለቱም የሰጡት አስተያየት ስህተት እንደሆነ ይነግሩናል። አያይዘውም ለእነኝህ ስህተቶች መፈጠርም ዋና ተጠያቂው አበራ ነው ይላሉ።ታሪኩ ምን ሊሉን ነው የፈልጉት? አበራ የሚጠየቁት በጽሑፋቸው ነው ወይስ ሌሎቹ የተሳሳተ ኣስተያየት በመስጠታችው ነው? ወይስ አበራ ተሳሳቱ አሏቸው ነው የሚሉን? ታሪኩ ዝም ብለው አበራን አላግባብ መቃወም ስለፈለጉ ብቻ ሌሎችንም ያሳሳተ እርሱ ነውና እርሱ ማለት የአጥፊዎች ኣጥፊ ለማለት እየዳዱ እንደሆነ ዐረፍተ ነገሮችዎ ይናገራሉ። አካሄድዎ ”ሊበሏት የፈለጓትን አሞራ ስሟን የሏታል ዥግራ” መሰለኝ ሳጤነው። ሲሰባሰብ ታሪኩ የሚሉን አበራም ሁለቱ አስተያየት ሰጭዎችም ስህተተኞች ናቸው ነው። ታድያ ማን ነው ትክክል? ሲባሉ ”ዘራፍ! ታሪኩ ኣባዳማ ነዋ!…” ሊሉን መሰለኝ። እናንተ ሁለታችሁም ትክክል ኣይደላችሁም ብሎ አስተያየት ለመስጠት መጀመር እኔ የምለው ብቻ ነው ትክክል እመኑኝ ለማለትና ትኩረት ለመሳብ የምታገለግል ቀቢጸ ተስፋዊ አቀራረብ ናት። ይህቺ እኔ ብቻ ያልኩት ይሁን አባዜ የተዋሃደችዎ ቀድሞ ይሰሩበት ወይም ……. ከነበረው የህዝብ ድርጅት ጉዳይ ጊዜያዊ ጽ/ቤት ሳትሆን ኣትቀርም። ችግር ነው ከአብሮ ኣደግ ጋር ኣትሰደድ ይባል የለ ።ታሪኩ አይዞን ለትዝታ ያህልና ትንሽም ላስቅዎ ብዬ እንጅ አንዳንዶቹ አንደሚያስቡት ባለፈ ታሪክዎ ለማስፈራራት አይደለም አባ። ደግሞስ በስደት ዓለም ማን ፈሪ ማን አስፈራሪ ሊሆን ይቻለዋል? እንዳው ታሪክን መዝለል አይቻለምና ነው ማንሳቴ። ይህንን ማንሳቴ ካስቀየመዎ ደግሞ ታላቅ ይቅርታ።

 

*** በመቀጠልም አቶ አስፋው ዳምጤ የበዓሉ ግርማ ከስራ መታገድ ሳያስፈራቸው እቤቱ መመላለሳቸውን የሚጠቅሱት ታሪኩ አባዳማ በዓሉ ደብዛው ከጠፋ በኋላ እርሳቸውም አብረው ቢጠፉ አይፈረድባቸውም። ፈርተውም ሊሆን ይችላል ይሉናል። መጽሐፍ ጽፈሃል ተብለው ከስልጣናቸው ከታገዱት ከጓደኛቸው ጋር ሳይፈሩ መለኪያ ሲያነሱና በቤታቸው ሲመላለሱ የነበሩት ሰው ጓደኛቸው ጭራሹኑ ደብዛቸው ሲጠፋ የአፋልጉኝ ጩኸት ማሰማት ሁኔታው ባይፈቅድላቸው እንኳን ወደቤቱ ሂደው ቤተሰቡን መጠየቅ ምን ያስፈራቸዋል ተብሎ ቢጠየቅ መልስ የሚፈለገው ከራሳችው ከኣቶ አስፋው ዳምጤ እንጂ ከታሪኩ አባዳማ ሊሆን አይችልም። በርግጥ በስርዓቱ የነበረ እንደሚያውቀው ሁሉ እንኳን አንድ ትልቅ ባለስልጣን ቀርቶ፣ ተራ ሰው ቢሆንም በመንግስት ሲታፈን ሁሉም እንደሚሸሽ የታወቃል። ሆኖም ግን ቤተሰባችውን ምን ያሸሻል? በባህላችንም የአንድ የቅርብ ጓደኛ ቤተሰብ እንዲህ ባለ ክፉ ቀን ሀዘኑና ፀፀቱ የማይጠፋ፣ አልቅሶ መቅበር እንደጸጋ ሆኖበት ይህን ለተነፈገ ቤተሰብ በቅርብ ማጽናናት ከቅርብ ጓደኛ በጣሙን የሚጠበቅ ነበር። ከበዓሉ ግርማ ታፍኖ መጥፋት በኋላ ደረጃው ባይበዛባችውም የኩራዝ አሳታሚ ድርጅት ም/ዋና ሥራ አስኪያጅ ለመሆን የቻሉት አቶ አስፋው ዳምጤ ታሪኩ ሊንግረን እንደሚሞክረው ብዙ አይዳፈሩት እንጅ ብዙም አይፈሩትም። ለምን ቢባል ከዛ በፊትም የደርጉ ቋሚ ተጠሪ ሆነው ለቤተ መንግስቱም ሆነ ለባለስልጣናቱ ባዕድና እንግዳ አልንበሩምና። ስለሆነም ፈርተው ቀሩ አይመስልም። ባህላችንን ሰብረው እንደሸሹ ቀሩ አይዋጥም። እናም ሀቁን ራሳቸው በህይዎት ያሉት ወይም ታሪክ አንድ ቀን ጭብጥ ያለው ማብራሪያ ይሰጠን ይሆናል የደራሲ አበራ ጥያቄም ዝም ኣትበሉ ነውና። የአሟሟቱን ታሪክ እንጅኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን በዓሉን ካጣነውማ ሦስት ኣሰርቶች ተቆጠሩ እኮ።

 

*** ” በዓሉን የበላውማ ደርግ የሚባል ዥብ ነው። ታሪኩ ኣባዳማ! አሁን አበራ ላቀረቡት የአሟሟት ጥያቄ ይኼ መልስ የሆናል ብለው ነው?   ”የትኛው ዥብ ነው የበላቸው? ምነው አልጮህ አለ?” እኮ ነው መሰረታዊ የአበራ ጥያቄም። የሚያውቁት ጉዳይ ካለ ኦፐሬሽኑን ያብራሩ ካላወቁ ዝም ብለው ሌሎች የሚያውቁ እስኪያገልጡልን ድረስ ይጠብቁ። እርስዎ እኮ ስለጉዳዩ የሚያውቁ ሰዎች መልስ እንዳይሰጡ ደርግ የሚባል ዥብ ነው የበላው እያሉ በጥቅል መልስዎ ኣገር ባወቀው ፀሐይ በሞቀው እውነታ ያላዝኑብናል።ደርግ እኮ አንድ መቶ ሀያ ያህል አባላት የነበሩት መንግስታዊ አካል ነበር። ታሪኩ በእውነት እልዎታለሁ በዓሉን የበላውማ ደርግ የሚባል ዥብ ነው ብሎ በተራ አገላለጽ ማለፍ ምጻታዊ አገላልጽና በትክክልም በሟቹ ቤተሰብና በኢትዮጵያ ሕዝብ የፍትህ ጥያቄ ላይ ማፌዝ ነው። ከዛም ሲያልፍ የበዓሉን ታሪክ አረም በማልበስ ለገዳይና ኣስገዳይ በጨረቃ ጥላ ዘርግቶ ማሽቃበጥ ይሆናል። ከዚህ አድርጎትዎ ጋር አንድ የሚስማማ የአባቶች የአንጋገር ፈሊጥ ትዝ አለኝ ”ስልብ አሽከር በጌታው ብልት ይፎክራል ” የሚለው።

 

*** መመኘት ወንጀል አይደለም። በጣም የሚመቸኝ ውብ አባባል ነው።ታሪኩ ጥሩ ብለዋልና እኔም እስማማበታለሁ። ስለሆነም ታዋቂው ጋዜጠኛ አቶ ሙሉጌታ ሉሌ ከመምሪያ ኃላፊነት የም/ሚኒስትርነት ደረጃ ቢመኙ ወንጀል ሊባል ኣይችልም። የሰው ልጅ በተፈጥሮው ከፍ እያለና እየተሻሻለ መሄድን እንጅ ወደታች መውረድና ቁልቁል መሄድን አይመኝም። አይመርጥምም። ስለሆነም አባባልዎን ተቀብያለሁ ብልም አንዳንድ ነጥቦችን ግን ማመላከት እፈልጋለሁ። እንደተባለው በማናችውም መልኩ ቢፈተሽ የሰው ልጅና ምኞት ተለያይተው አያውቁም። እንዳውም ፈረንጆቹ በጥናት እንዳረጋገጡት ከሆነ የሰው ልጅ አንደኛው ፍላጎቱ ሲሟላ ከመቅጽበት ሌላኛው ይተካል ይላሉ። በራሳቸው አባባልም Theory of Need says ” When one of your need is satisfied immediately the other replaces. “ እንግዲህመመኘትከሰውልጅጋርየተሳሰረናተፈጥሯዊምይሁንእንጅበውስብስቡየህብረተሰብክንዋኔውስጥመንፈሳዊእናእርኩሳዊገፅታይታይበታል። ለምሳሌተምሮራስንትልቅቦታለማድረስምሆነበዕውቀትናበስራጎልብቶእድገትንመመኘትክፋትየለውምናመንፈሳዊምኞትልንለውእንችላለን።በአንጻሩምበአግድሞሽመስፈርትተሸጋግሮያለብቃትናያለችሎታከደረቅፍላጎትብቻተነስቶከሁሉምበላይበሌላውአንጀራናሕይወትጣልቃበመግባትናበኣቅርቦሽብቻደረጃንለማሳደግየሚደረግሩጫበኣጠቃላይየአንዱንሕይወትኣበላሽቶየራስንምኞትለማሳካትየሚደረግማናቸውምምኞትእርኩሳዊምኞትከመባልኣያልፍም።ስለዚህኣቶታሪኩእንዳሉትመመኘትበራሱጥፋትምሆነወንጀልሊባልአይችልም። ይህምስለተባለአንዳንድሰዎችተሳስተውከሆነአጠቃላይባህርይባለውምኞትሽፋንልንከላከልላቸውብንሞከርሌላስህተትመስራትይሆናልናየብይንሚዛናችንንበጥንቃቄእንያዘውእላለሁ።

 

በአጠቃላይኣቶታሪኩኣባዳማየደራሲበዓሉግርማንአሟሟትአስመልከተውአቶአበራለማያቀረቡትንጭብጥአዘልጥናታዊ ጽሑፍኣሳንሰውናደረጃውንምወደመስርያቤትሽኩቻዝቅአድርገውበአለቃናምንዝርቅራኔብቻወስነውታል።ይህበፍጹምስህተትነው። የብዙሃኑየውስጥሕሊና እሾህሆኖለሚኖረውግፋዊአገዳደልጥያቄ፣ለተጎዳ ህሊናእረፍትሲሉጉዳዩንየሚያውቁትእንኳንእንዳይናገሩመስረታዊየሆነውንጥያቄወደጎንበማስቀመጥ፣በኣቶሙሉጌታሉሌእናበኣቶአበራለማአለመጣጣምየተፈጠረተራጉዳይአስምስለውማቅረብዎከአንድጋዜጠኛነበርኩከሚለንባለሙያኣይጠበቅም።የሚወዷቸውናየሚያከብሯችውግለሰቦችስምተጠቀሰብለውያቀረቡትትችታዊአስተያየትአንኳርጥያቄውአረምእንዲበላውናይህምአልቅሶበመቅበርመጽናናትንላጡትለበዓሉግርማቤተሰብትልቅየሞራልድቀትንያስከትላልበማለትባቀረቡትጽሑፍከልብማዘኔንሳልደብቅልገልጽልዎትእሻለሁ።

 

 

.የተስፋዬተሰማትችትናየኔምልከታ

 

***ሲጀመርጽሑፋቸውበጣምድግግሞሽ / redundancy / ስለሚበዛበትበአንድቦታላይመነሻብለውየሚያቀርቡትሃሳብሌላቦታላይውጤትሆኖይቀርባል።ሌላቀርቶበአንድነጠላአንቀጽውስጥሲጅምሩይገነቡትናፍጻሜውላይሲደርሱደግሞያፈርሱታል።ለምሳሌይህንአባባላቸውንእንየው…

 

“ ለዚህየውሸትክስአሁንምኣስፋውዳምጤንበቅርቡከሚያውቁሰውየሰማሁትወ/ሮአልማዝ

(የበዓሉባለቤት ) እናደራሲአስፋውዳምጤበአቶበዓሉጉዳይተገናኝተውአውርተዋል።

በመሃላችውየተፈጠረቅሬታአለ።እሱንደግሞአስፋውዳምጤእንደአበራለማስላልሆኑ

እውነቱንእንደጥላሁንገሠሠሆድይፍጀውብለውየሚሉይመስለኛል። ህዝብይወቀውብለው

የራሳቸውንእውነትቢያወሩጥሩነው። “ ይላሉ፡፡

Be`alu Girma

Be`alu Girma

 

ተመልከቱእንግዴህ ሆድይፍጀውብለውዝምማለታችውንመጀመሪያላይአበጁይሉናወረድብለውደግሞእውነቱንሕዝብእንዲያውቀውቢናገሩጥሩነውይሉናል።በዚህአካሄድእኮአቶአበራለማምያሉትሆድይፍጀውብላችሁዝምአትበሉየምታውቁሰዎችየምታውቁትንንገሩንነው።ታድያምኑላይነውያቶ አበራ ስህተት? የምታውቁሰዎችየምታውቁትንተንፍሱየሚለውየኣበራጥሪየግድበጽሕፋቸውላይስማቸውንየጠቀሱትንግለሰቦችብቻአይመለከትም።ጉዳዩከቀድሞውየሀገሪቱመሪከኮ/ልመንግስቱኃ/ማርያምጀምሮበየደረጃውየነበሩትንየፓርቲናየመንግስት ባልሰጣናትንየሁሉየሚያካትትነው።ይህንማለትደግሞውሸታምእብድሞኝአስመሳይሴረኛ ….. አስብሎዘላንኛ የሚያዘልፍምክንያት ጭርሱኑ ሊኖር አይችልም፡፡በግል ያለግላዊጥላቻካልሆነበስተቀርየጥያቄውሁለንተናዊ እውነታ መነሳቱ ከቶም ሊነወር አይገባውም፡፡

 

*** በአንድበኩልበዓሉንየመሰለታላቅሰውእንደዋዛደብዛውጠፍቶመቅረቱያሳዘናቸውአቶተስፋዬበሌላበኩልደግሞሰለበዓሉአሟሟትየሚጠይቀውንጽሑፍሲኮነኑይታያሉ።ለዚህእውነታራሳቸውበራሳቸውአገላልጽያሰፈሩትንቀጥለንአንመልከት፡፡

 

በዓሉግርማንየሚያክልበኢትዮጵያጋዜጠኝነትናስነጽሑፍታላቅቦታየነበረውሰው

እንደዋዛወጥቶመቅረቱወይምያለበቂምክንያትመገደሉየሁላችንምሀዘንናየልብስብራት

ነው።የዚህንታላቅሰውየአገዳደልምስጢርማወቅናለማወቅጥረትማድረግመቀጠል

ያለበትበመሆኑሁሉምወገንኃላፊነትእንዳለበትእሙንነው። “ ይላሉደሞለማለት!

 

አቶተስፋዬታድያአበራለማስለበዓሉግርማአሟሟትቢጽፉለምንየስድብውርጅብኝያወርዱባቸዋል? ነውወይስጥያቄውንእርስዎናመስሎችዎሲያነሱትሰብአዊናመንፈስዊአበራሲጠይቁትግንከመቅጽበትግላዊናእርኩሳዊይሆናልሊሉንእየሞከሩነው? ይህአመለካከትዎሩቅአይደለምአንድፈርማታአይስኬድዎምናበበዓሉጉዳይከኣበራጋርሣይሆንከራስዎጋርቢታገሉና እርቅ ቢፈጥሩሸጋነው።ደግሞስበበዓሉጉዳይምንአለያያችሁ? እርስዎየሚሉት ( ከልብከሆነ! ) የበዓሉጉዳይየሁላችንምስለሆነአገዳደሉንለማወቅጥረትማድረግአለብንነው፡፡እግዜብሔርይባርክዎ። አበራምያሉትበዓሉንየበሉዥቦችምነውአልጮህአሉ? ነውእግዚኣብሔርይባርካቸው።ታድያአበራለማንናተስፋዬተሰማንምንያለያያቸዋል? የበዓሉአሟሟትየይታወቅጥያቄ ? NO. NO. NO. ምናልባትየግልጥላቻ? የማውቀውጉዳይየለም። ግን ከጤነኛ አእምሮ ለመመንጨቱ እጠራጠራለሁ፡፡

 

እንዳውምአቶተስፋዬቀጠልያደርጉና”……..በዚህቅኝትየተጻፉጽሑፎችበህዝቡውስጥሲሰራጩየበዓሉንአሟሟትምስጢርየበለጠውሉንእያጠፋውናእያወሳሰበውይመጣልየሚልስጋትአለኝ”ይላሉ።የአበራጽሑፍእኮግልጽና በየትኛውም ደረጃ ያለ ሰው አንብቦ በሚረዳው መደበኛ ያማርኛ ቋንቋ የቀረበ ነው፡፡ እንደርሶ ያለ የተምታታበት ሰው በራሱየተምታታበትካልሆነበስተቀርማንንምአያምታታም።እርስዎምአኮተርድተውናገብቶዎት “ የበዓሉጉዳይየሁላችንምነው! “ ብለውብይንዎንአስፍረዋል።አይዞንአይፍሩበበዓሉጉዳይደንታየለውምየሚለዎየለም።ደግሞስሰውያሻውንቢልማንነትዎንአይለውጠው፣ጠንከርነው እንደ በረህኚቱ ሰጋር ግመሊቱ!!!!

 

*** ወንጀልናወንጀለኛነት

 

“ ከወንጀሎችሁሉወንጀልወንጀለኛያልሆነንሰውወንጀለኛማለትነው“ በጣምየሚመቸኝየኣቶተስፋዬአባባልነው።እኔእንደገባኝከሆነአበራበግልጽነትያሰፈሩትገዥሀሳብውንጀላአይደለም።

የበዓሉአሟሟትእስከመቼምስጢራዊሆኖይደበቃል? እባካችሁየበላችሁትምሆነሲበሉትያያችሁድምጽችሁንአሰሙንሌላቢቀርንስሐግቡአይነትይመስለኛል።ደራሲ አበራ ከተለያዩ ምንጮች ያገኛቸውን ማስረጃዎች እየጠቀሰ፣ የሚመለከታቸውን ሁሉ ያለው መልስ ስጡ እንጂ አቃቤ ሕግ ሆኖ ልፋረዳችሁ አይደለም፡፡ በመሆኑምእገሌእናእገሌበበዓሉአሟሟትወንጀለኞችናቸውየሚልአንድምገላጭጭብጥየለም።ያለማስረጃ በሃሰትግለሰቦችንወንጅለውጽፈውከሆነተወንጃዮቹበህግየመክሰስ፣ወንጃዩምበህግየመከሰስመብትናገዴታአለባቸው።ደግሞስ“አንድ ሰው ወንጀለኛነቱ በህጋዊ የፈርድ አካል እስካልተረጋገጠ ድረስ በህግ ፊት ወንጀለኛ አይሆንም“የሚለውን ሁለንተና ድንጋጌስ አቶ ተስፋዬ ሳይውቁት ቀርተው ነው ወይስ የኣዞ እንባዎ እየፈሰሰ ኣስቸገረዎት ? ከዚህ የወንጀለኛ ፍረጃዎ ሳንወጣ በራስዎ ጽሑፍ ራስዎንም ወንጀለኛ አድርገው ያቀረቡበትን አገላለጽ ላስታውስዎ እፈልጋለሁ ከይቅርታ ጋር – “የበዓሉ ግርማ አሟሟት ጉዳይ የሁላችንም ነው” ካሉ በኋላ ይህን ይሽሩና መልሰው “የበዓሉን ስም እየጠቀሱ የበዓሉ ጠበቃ ነኝ ማለት በአዓሉን እንደገና የመግደል ያክላል” ይላሉ። እንግዲህ አርስዎም የበዓሉን ስም ጠቅሰዋልና ወንጀለኛ ነዎት ብለን በመፈረጅ አለም አቀፍ ፍርድ ቤት አናቅርብዎ ?… ኧረ አየተስተዋለ !

 

*** የጽሑፍ ደረጃ አመዳደብዎና የሙያ ብቃትዎ

 

“… አቶ አበራ ያቀረቡት በእውነተኛ መረጃ ድርቅ የተመታ በመሆኑ እንደ አጭር ልብ ወለድ መለካቱ የተሻለ ሆኖ አግኝቼዋለሁ። የሚያሳዝነው ነገር ጽሑፉ አንደ ልብ ወልድ ቢወሰድ እንኳን ደካማ ከሚባሉት የልብ ወለድ ጽሑፎች የሚመደብ ነው” ይላሉ። እንዴት ያለ ደረጃ ምደባ እንደሆነ አልገባኝም’፡፡ መጀመሪያ አንድን ስነ ጽሑፍ አጭር ልብ ወለድ፣ ረጅም ልብ ወለድ ብሎ ለመፈረጅም ሆነ ይዘቱን መርምሮ ደረጃ ለመስጠት የፍላጎት ሳይሆን የሙያ ባለቤትነትን ብቃት ይጠይቃል። ጠንካራና ደካማ ስነ ጽሑፍን ለመመዘን የሚያገለግሉ ቁልፍ መፍቻዎችን / key devices / ማወቅ በጣሙን ያስፈልጋል። ይህ የስሜት ሳይሆን የሙያ ጉዳይ ነው። በስሜት ተንስተውማ ጋዜጠኛና ደራሲ አበራን አንዴ የቀይ ሽብር ተከሳሽ ሌላ ጊዜ ደግሞ የኢህአዲግ ቀላጤ አድረገው ስለዋቸዋል። ችግሩ እርስዎ እራስዎ ካዲስ አበባ ፎርጅድ አሰርተው አምጥተው በኢትዮሚዲያ ፎረም አማካኝነት ካስበተኑት አሉባልታ ባሻገር ያየነው የለም፡፡ የምስራቁ ድል በሰሜኑም ይደገማል በሚለው የያኔው መርህ መሰረት ብሔራዊ አንድነትን ለማስከበር የዘመተ ዘማች ጋዜጠኛን፣ ተስፋዬ እንደሚሉት ደግሞ በቀይ ሽብር ተዋናይ የሆነን፣ ባለፈው መንግስት ደራሲና የፕሮፖጋንዳ ሠራተኛ ሆኖ ያገለገልን ሰው ወዘተ… በምን መስፈርት ነው የኢህአዲግ ቀንደኛ ተሟጋች ተብሎ የሚፈረጀው? መልሱ አንድ ነው – በስሜት ፈራጆች ዘንድ – ጠለሸት መቀባት!!

 

ውድ አንባቢዎች ! አቶ ተስፋዬ አቶ አበራን በቀይ ሽብር እንዴት ሊመድቧቸው ቻሉ? የሚለው ጥያቄ ምላሽና ትክክለኛ ታሪኩን ማውቅ ያስፈልጋል። እኔም ጉዳዩን እንዲህ ነው የተረዳሁት ሁለቱም ግልሰቦች ማለት ወንጃይና ተወንጃይ በየፊናቸው ያወጧቸውን ማስረጃ ከተመለከትኩ በኋላ ነው። ደንቆሮ የሰማ ዕለት ያብዳል ይባል የለ! ጭብጡ አንዲህ ነው….

 

አቶ ተስፋዬ አቶ አበራን በቀይ ሽብር ለመወንጀል ስለፈለጉ ጠቅላይ አቃቢ ህግ የሚገኝ ባለ 46 የተከሳሽ ተጠርጣሪዎች ስም ዝርዝር ያለበት ሰነድ አፈላልገው ያገኛሉ። በዚህ ዝርዝር 27ኛ ላይ “አበራ በሪሦ” የሚባል ተከሳሽ ተጠቅሷል። “አቶ ተስፋዬ” በመደለዝና ኮፒ ኤንድ ፔስት የሚባለውን ቴክኒክ በመጠቀም “…. በሪሦ” በሚለው ያባት ስም ምትክ “… ለማ” የሚለውን ተክተው፤ ኖርዌይ፣ አምስተርዳምና ቤልጂየም ወዘተ… ለሚገኙ ወዳጆቻቸው ይበትናሉ፡፡ በእዚሁ የክስ ፋይል ሌሎች ገጾች ላይም “ አበራ በልሁ” እና “አበራ በሪዮ” ተብሎ የተጠቀሰን የተከሳሽ ያባት ስም “በልሁ”ን በ“… ለማ” በመተካት አብረው አያይዘው ይልካሉ፡፡ “አቶ ተስፋዬ” እነዚህን ፎርጅድ ሰነዶች ያደረሷቸው ወዳጆቻቸው እውነተኛ መስሏቸው ካንዱ ወዳንዱ ሲቀባበሉ፣ አንዱ ሀቀኛ ሰው ላቶ አበራ ፎርጅዱን ሰነድ በማቀበል እራስክን ጠብቅ ይላል፡፡ ልብ በሉ ይህን ያዩት ደራሲ አበራ ለማ ደግሞ አርፈው ከተቀመጡበት የስደት ሕይወታቸው ተነስተው፣ “ይህን ቅሌታም በሃቅና በማስረጃ ማንበርከክ አለብኝ!…” ብለው ወደ አዲስ አበባ ለመጀመሪያ ጊዜ በረው የሄዱና “አቶ ተስፋዬ” አዘጋጅተው የበተኑትን ፎርጅድ ሰነድ ለጠቅላይ አቃቢ ህግ አቅርበው ጉዳዩ እንዲጣራላቸው ይጠይቃሉ፡፡ ጠቅላይ አቃቤ ሕግም ጥቄያቸውን ተቀብሎ ፎርጅዱን ከዋናው ሰነድ ጋር ሲያስተያየው ጭርሱን የማይገናኙ መሆናቸውን ላቶ አበራ ይገልጽላቸዋል፡፡ አቶ አበራም የዋናው ሰነድ ትክክለኛ ቅጂ እንዲሰጣቸው በጠየቁት መሰረት፣ ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ኮፒ አድርጎና ማህተም መቶ የሰጣቸውን ኦሪጅናል ሰነድ ይዘው ወደ ኖርዌይ ይመለሱና ለወዳጆቻቸው ሁሉ እንዲያውቁት ያሰራጩታል፡፡

 

“አቶ ተስፋዬ”ም በድርጊታቸው አፍረውና ተሸማቀው አንገታቸውን ደፍተው ከዚያ ወዲሀ ድምጻቸው ሳይሰማ ኖረዋል፡፡ ሰሞኑን ግን የበዓሉ ግርማን ጉዳይ ለማዳፈንና የደራሲ አበራን እውነት የማውጣት ጥረት ለማምከን ሲሉ ዳግም ይህን ያጭበረበሩበትን ሰነድ እየጠቃቀሱ ጉሮ ወሸባዬ ሲሉ ተስተውለዋል፡፡ “የሌባ ዓይነ ደረቅ መልሶ ልብ ያደርቅ” እንደሚባለው፣ አቶ ተስፋዬ ነጻነታቸውንና እውነትን ፍለጋ ወደ አገር ቤት የተጓዙትን አቶ አበራን “አገር ቤት ተመላላሽ ወያኔ ሆኗል” ይሉናል፡፡ እውን አቶ ተስፋዬ እርስዎና ቤተሰብዎ አገርዎ ደርሰው ሲመለሱ “ ወያኔ ሆኑ” ቢባሉ ፍትሃዊ ነው ይላሉ? ኢትዮጵያ የሚመላለሰውና የሚኖረው ሁሉ “ወያኔ” ከተባለ ታዲያ ምን ተረፈን? ወያኔን ባልተጠረበ ፐሮፓጋንዳዎ በጣም በጣም እየረዱት እንዳለ ያስተዋሉት አልመሰለኝም፡፡ አቶ አበራ ነጻነታቸውን ለማረጋገጥና በሕዝብ ፊት ሳይሸማቀቁ ለመቆም በራስ ተማምነው እንኳን አገራቸው የትስ ቢሄዱ በምን መመዘኛ ነው የሚነቀፉት? አይ “አቶ ተስፋዬ” ይህን ስምዎን በእውነተኛ ስምዎ በመምሬ አብደላ ቢቀይሩት ያሻል ነበር፡፡ እሺ ይዋሹ ላንዴ – ለዘለኣለሙ ግን ሕሊናን ዋሽቶ መኖር እንዴት ይቻላል?እኔም በቅርቡ አንድ ሰው በፌስቡክ ላይ ከለቀቀው ማሳሰቢያ ይህንን የፎርጅዱንና የኦሪጂናል ሰነዱን ምንና ምንነት ከነማብራሪያው ለመረዳት በመቻሌ በ”አቶ ተስፋዬ” አሳፋሪ ተግባር በጣሙን አፍሬያለሁ ፡፡ ላንባቢዎቼም ለማካፈል ፈቅጃለሁ፡፡

 

ስለዚህ “አቶ ተስፋዬ”ን መሰል በሬ ወለደ ባዮች ይሁን ብለው ሌላውን እንዳያሳስቱ ትምህርት ይሆን ዘንድ ቀጥሎ ሰነዶቹን በቅደም ተከተል አስቀምጫቸዋለሁ፡፡ በዚህም ውድ አንባቢዎቼ እውነተኛ ፍርዳችሁን ትሰጡ ዘንድ እጠይቃለሁ፡፡

 

  1. በ”አቶ ተስፋዬ” የተሰናዳው ፎርጅድ 1ኛ

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

  1. በ”አቶ ተስፋዬ” የተሰናዳው ፎርጅድ 2ኛ

 

 

 

 

 

 

  1. ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ላቶ አበራ ለማ ማረጋገጫ የሰጠው ኦሪጂናል ቅጂ 1ኛ

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

  1. ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ላቶ አበራ ለማ ማረጋገጫ የሰጠው ኦሪጂናል ቅጂ 2ኛ

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

  1. ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ላቶ አበራ ለማ ማረጋገጫ የሰጠው ኦሪጂናል ቅጂ3ኛ

 

 

 

ማጠቃለያ

 

ደራሲ በዓሉ ግርማ በፈጠራ ክሂላቸው ለሀገራችን የስነ-ጽሑፍ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጾ በማድረጋቸው በዘርፉ ብሔራዊ እውቅናንና ክብርን ካገኙ አንቱ የተባሉ ደራስያን አንዱ ናቸው። በነበራቸው መንግስታዊ ስልጣንም አገራቸውንና ህዝባቸውን በቅን በማገልገላቸው የህዝብ ፍቅር ነበራቸው። ምንጊዜም ቢሆን ያመኑበትን ጉዳይ ከማድረግ አንዳችም ቁጥብነት ያልነበራቸው በዓሉ ግርማ የሀገራችንንና የቱባ ቱባ ባለስልጣናቱን ጉድፍ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳየው መጽሀፋቸው “ኦሮማይ” ለደብዛቸው መጥፍትና በግፍ ለመገደላቸው ዋና ምክንያት እንድሆን በድፍን ኢትዮጵያ ይታወቃል። በዓሉ በግፍ ታፍነው በድኑ አካላቸው ከምድር በታች ቢሆንም ለኢትዮጵያውያን ግን በአዓሉ ምንም ጊዜም በህይወት አሉ፣ ይኖራሉ። እጅግ በተመረጡ ቃላት ታጅበው ልብን በመስቀል የማይረሱቱ ድንቅዬ መጻሕፍቶቻቸው ምን ጊዜም ቢሆን የአሟሟት ታሪካቸውን ሁሌም እንድንጠይቅ ያነሳሱናል። ይህ ሁሌም የህዝብ ጥያቄ የሆነውን የደራሲ በአዓሉ ግርማን የአሟሟት ታሪክ የማወቅ ጥያቄ አስመልክተው ጋዜጠኛ አበራ ለማ አንድ ጽሁፍ ስለዘከሩን ግላዊ ምስጋናዬ ይድረስዎ። ይህን ጽሁፍ አስመልክተው አንዳንዶቹ የሰጡትን አስተያየት ግላዊ ፍተሻ በማድረግ በሚከተሉት ነጥቦች አስተያዬቴን እቋጫለሁ።

 

  1. በኣቶ አበራ ጽሑፍ ላይ ስማቸው የተጠቀሱት አቶ ሙሉጌታ ሉሌ እና አቶ አስፋው

ዳምጤ ሁለቱም የዕድሜ ባለፀጋ ብቻ ሳይሆኑ በሙያም የበለጸጉና ሀገራቸውንም

በሙያቸው ያገለገሉ አንጋፋ ሰዎች ናቸው። ከሁሉም በላይ ደግሞ ለሚቀርብባቸው ማናቸውም ጉዳይ ራሳቸውን ችለው መቆም ስለሚችሉ 3ኛ ወገን አዛኝና ተቆርቋሪ

መስሎ በአቶ አበራ ላይ ያለና የቆየ የግል ቂምን ለመወጣት መሞከር ኢ ሞራላዊ ስለሆነ ሊታረም ይገባል አላለሁ።

  1. ደራሲ አበራ ለማ ማንነቱን ሸሽጎና የብዕር ስም ተጠቅሞ የሚፈልገውን አስተያየት መጻፍ ይችል ነበር። ይህን ያልመረጠበት ግን አንድ ሀቅን ይገልጻል። ይህም አግባብ ያለው ትችም ከመጣ ይምጣ እንደ አመጣጡ እኔው ለጻፍኩት እኔው ነኝ ኃላፊው ብሎና ደፍሮ ነው። ይህ የአበራ ጽሑፍ እንዳለ በሌላ ስም ተጽፎ ቢሆን ኖሮ ታሪኩ አባዳማም ሆኑ ተስፋዬ ተሰማና ሌሎች ካቶ አበራ ጽሑፍ ጋር ምንም ዝምድና የሌለው እሪ በከንቱ ጽሁፍ የጻፋችሁ ሁሉ፣ መልስ ከመስጠት ትቆጠቡ ነበር የሚል ግምት አለኝ፡፡ የናንተ ድንበር ዘለል ወገንተኛነት ብዙ ሰዎችን እንዳሳዘነ ከኔ አይነቱ ምላሽ የምትረዱት ይመስለኛል፡፡

 

  1. አንድ አንድ ድህረ ገጾችም የአበራን የውይይት መነሻ ጽሑፍ ሳያወጡ ነገር ግን ፈጥነው

የተሰጡ ምላሾችን ማውጣታቸው ትዝብት ላይ ጥሏቸዋል። በአናቱም አንባቢዎች ቅደም ተከተል ያለው እሰጥ እገባን በሚገባ ተከታትለው ወደ ትክክለኛ ብይን አንዳይንደረደሩ ትፅዕኖ አሳድሯል፡፡ ህዝብ ትክክለኛ መረጃ የማግኘት

መብት አለው የሚለውን መሰረታዊ አባባልም መሸርሸር ይሆናልና ለወደፊቱ

ብርቱ ጥንቃቄ ይደረግ በማለት አንባቢዎቼን እሰናበታለሁ።

 

sirakyoftahe@gmail.com

 

 

 

 

 

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 10 years ago on September 8, 2014
  • By:
  • Last Modified: September 8, 2014 @ 6:15 pm
  • Filed Under: Ethiopia
  • Tagged With:

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar