www.maledatimes.com “የትግራይ አርሶ አደሮች በካድሬዎች መብታቸው እየተረገጠ ነው” - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

“የትግራይ አርሶ አደሮች በካድሬዎች መብታቸው እየተረገጠ ነው”

By   /   March 31, 2014  /   Comments Off on “የትግራይ አርሶ አደሮች በካድሬዎች መብታቸው እየተረገጠ ነው”

    Print       Email
0 0
Read Time:45 Second

 

አበባየሁ ገበያው

31 March, 2014

በነገው እለት በትግራይ ክልል በእንደርታ ኪዊሃ፣ ህዝባዊ ስብሰባ እንደሚያካሂድ የገለፀው ዓረና ፓርቲ፤የትግራይ አርሶ አደሮች በካድሬዎች መብታቸው እየተረገጠና እየታፈነ ነው አለ፡፡

95 ፐርሰንት ያህሉ አርሶ አደሮች ከብድር ተቋማት ከ5ሺ እስከ 30ሺ ብር ብድር መውሰዳቸውን ከአንድ ጥናት መረዳታቸውን የጠቆሙት የፓርቲው ሥራ አስፈፃሚ አቶ አብርሃ ደስታ፤ ዓረና ለመጪው ምርጫ የፓርቲውን ፕሮግራም ለማስተዋወቅ በተዘዋወረባቸው የገጠር ክፍሎች አርሶ አደሮቹ በወሰዱት ብድር የተነሳ  መብትና ነፃነታቸው እየታፈነ መሆኑንና ክፉኛ እንደተማረሩም ተናግረዋል፡፡

የዓረና ፓርቲ አመራሮች ህዝባዊ ስብሰባ ባደረጉባቸው ሰባት የገጠር ክፍሎች፣ የትግራይ አርሶ አደሮች በማዳበሪያ ዕዳና በብድር በመያዛቸው ህወሐትን የሚቃወሙ ከሆነና በዓረና  ስብሰባ ላይ ከተገኙ፣ ዕዳችሁን ክፈሉ እየተባሉ መውጪያ መግቢያ እንደሚያጡ አቶ አብርሃ ገልፀዋል፡፡ በዚህም የተነሳ ነፃነት ተነፍገው ከህወሐት በቀር ሌላ ፓርቲ እንዳይደግፉ መብታቸውን ተነፍገዋል ብለዋል፡፡

ባለፉት  ወራት ከሳዑዲ ከተመለሱ ኢትዮጵያውያን መካከል አብዛኞቹ በትግራይ ክልል የሚገኙ ወጣቶች እንደነበሩ የጠቆሙት የፓርቲው ሥራ አስፈፃሚ፤ የስደት ተመላሾቹ “ለሥርዓቱ አደገኛ ናቸው” በሚል በመገለላቸው፣ አብዛኞቹ በእግርና በባህር እያቋረጡ ወደየመንና ሳኡዲ ተመልሰው እየተጓዙ ነው ብለዋል፡፡

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 10 years ago on March 31, 2014
  • By:
  • Last Modified: November 28, 2014 @ 4:22 pm
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar