Read Time:28 Second
በፀሐፊ እሙሼ የተፃፈው “የበረዶ ስር ፍሞች” ልብ ወለድ መፅሃፍ ዛሬ በገበያ ላይ ዋለ። አጭር ልብ ወለዶችንና አንድ ኖቬላ ታሪኮችን የያዘው መፅሃፍ በማህበራዊ ውጥንቅጦች ላይ ያተኮሩ ታሪኮች የተካተቱበት ነው።
“የበረዶ ስር ፍሞች” መፅሃፍ 172 ገፆች ሲኖሩት አስራ አንድ ታሪኮችን የያዘ ነው። ባለ አንድ መቶ ሰባ ሁለት ገፁ መፅሃፍ በአርባ ብር ለገበያ የቀረበ ሲሆን ይህ መፅሃፍ ለፀሃፊው ሁለተኛ መፅሃፉም ነው። ፀሃፊው ከዘጠኝ አመት በፊት “የጨለማ ግሳቶች” የተባለ መፅሃፍ አሳትሞ የነበረና በበርካታ ጋዜጦችና መፅሄቶች ላይ የሰራ ጋዜጠኛም ነው። ጋዜጠኛው ከሰራባቸው ጋዜጦች ውስጥ “አዲስ ልሳን”፣ “ዕለታዊ አዲስ”፣ “ዘ_ፕሬስ” ና “ማክዳ” መፅሄት ይገኙበታል።
Wondering where the comments are? We encourage you to use the share buttons below and start the conversation on your own!
- Email a link to a friend (Opens in new window) Email
- Share on Facebook (Opens in new window) Facebook
- Share on X (Opens in new window) X
- Share on LinkedIn (Opens in new window) LinkedIn
- Share on Pinterest (Opens in new window) Pinterest
- Share on Tumblr (Opens in new window) Tumblr
- Print (Opens in new window) Print



Print
Email
Average Rating