www.maledatimes.com ሳዑዲ አረቢያ ባስተባበረቻቸው 10 ሀገሮች አየር ሀይል ነው ጥቃቱ… - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

ሳዑዲ አረቢያ ባስተባበረቻቸው 10 ሀገሮች አየር ሀይል ነው ጥቃቱ…

By   /   March 27, 2015  /   Comments Off on ሳዑዲ አረቢያ ባስተባበረቻቸው 10 ሀገሮች አየር ሀይል ነው ጥቃቱ…

    Print       Email
0 0
Read Time:1 Minute, 19 Second

የመን ምጥ በቁና ሆና በአየር ስትደበደብ አደረች

በግሩም ተ/ሀይማኖት
ረቡዕ እለት ለሀሙስ አጥቢያ ከሌሊቱ 8፡30 አካባቢ የየመኗ ዋና ከተማ ሰነዓ በፍንዳታ ተናወጠች፡፡ ቀጥሎም የአነስተኛ እና ከባድ መሳሪያ ተኩስ ቀጠለ፡፡ የመጀመሪያው ፍንዳታ ከተሰማ በኋላ ደጋግሞ ቀጠለ፡፡ ሳዑዲ አረቢያ ካስተባበረቻቸው 10 አረብ ሀገራት ጋር በመሆን በ200 በላይ ጀቶች የአየር ድብደባ እያደረጉ ነው፡፡ የየመን መገናኛ ብዙሀን እና ሌሎችም ይህንኑ እየጠቀሱ ነው፡፡ ከዚያ በኋላ የነበረው ተኩስ እስኪነጋ ቀጠለ፡፡ የአየር ጥቃቱ የተደረገው በወታደራዊ ተቋማት ላይ ነው፡፡ የቀድሞው ፕሬዘዳንት አሊ አብደላ ሳላህ ቤትም መመታቱ ተነግሯል፡፡
ንጋት ላይ ግን የወትሮውን እንቅስቃሴ የቀጠለ ቢመስልም አልቀጠለም፡፡ ቀኑንም ጭር ብሎ እንቅስቃሴው ተገታ አልፎ አልፎ የተኩስ እና ከባድ መሳሪያው ከርቀትም ከቅርበትም ይሰማል፡፡ በአየር የሚደረግ ጥቃቱ ግን ከከተማው ውጭ እንደቀጠለ ነው፡፡ ከተማ ውስጥም ከሁለት ጊዜ ያላነሰ ቦታ በአየር ተመቷል፡፡
አሁን ምሽቱን ደግሞ በጣም በተጠናከረ ሁኔታ አሁን ተጀምሯል፡፡ ከአየር የሚጣለው መሳሪያ መሬት ሲያርፍ ከፍተኛ የሆነ ብርሃን አካባቢውን ያወርስና ወዲያው በጭስ የታጀበ እሳት እና አቧራ ይነሳል፡፡ እስካሁን ባለው ሁኔታ የተመቱት ወታደራዊ ተቋማት ብቻ ናቸው ቢባልም የተፈለጉ ሰዎች ቤት እና ቦታዎችም እየተመቱ ናቸው፡፡ ሰነዓ ያለ ሀበሻ በሰቀቀን አለቅን በሚል ፍርሃት ውስጥ መሽጎ ነው ያለው፡፡ በእርግጥ እንኳን እኛ ስደተኞቹ ባለሀገሮቹ የመናዊያኑም በከፍተኛ ፍርሃት ውስጥ ነው ያሉት፡፡ እግዚአብሄር ሆይ በብዙ ነገር የተገፋን ህዝቦች ነን በመንግስታችንም ተገፍተን ተደፍተን ነው ያለነው፡፡ አረቦቹ እንኳን ሲጫወቱብን ለምን የሚል መንግስት የለንም፡፡ ለመንግስት ባለስልጣኖችም ቀና ልቦና ለወገናቸው አሳቢነት ስጣቸው፡፡ ወገን ሊያልቅ ተጨንቆ እያዩ በዝምታ ተቀምጠዋል እና ችግሩን የሚያዩበት አይን ብቻ ሳይሆን የሚገነዘቡበት ልቦና ስጣቸው፡፡ ከሁሉ ከሁሉ ግን የአንተ ጥበቃ አይለየን አምላኬ፡፡……..
ኦ….. ፍጣሪ አምላኬ ስደተኛ ልጆችህን ጠብቅ በአሁኑ ሰዓት ሰነዓ በከፍተኛ ተኩስ ተናውጣለች፡፡ የአየር ድብደባው ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ የመናዊያኑ አንድ ጄት መጣላቸውን ይናገራሉ፡፡ እንደነሱ አባባል ከሆነ ከረቡዕ ሌሊት 8፡30 ጀምሮ እስካሁን 4 ጄቶች እንደጣሉ ነው፡፡

About Post Author

Abby

Internet reporter, freelancer and webmaster.
Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 9 years ago on March 27, 2015
  • By:
  • Last Modified: May 9, 2015 @ 5:44 pm
  • Filed Under: Ethiopia

About the author

Internet reporter, freelancer and webmaster.

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar