www.maledatimes.com የሰማያዊ ፓርቲው አመራር ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት በነገው እለት በችካጎ ከፍተኛ፡ስብሰባ ይመራሉ ተብሎ ይጠበቃል - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

የሰማያዊ ፓርቲው አመራር ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት በነገው እለት በችካጎ ከፍተኛ፡ስብሰባ ይመራሉ ተብሎ ይጠበቃል

By   /   April 18, 2015  /   Comments Off on የሰማያዊ ፓርቲው አመራር ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት በነገው እለት በችካጎ ከፍተኛ፡ስብሰባ ይመራሉ ተብሎ ይጠበቃል

    Print       Email
0 0
Read Time:56 Second

ለእረጅም ጊዜ በጉጉት በሰሜን አሚሪካ ይገባሉ ተብሎ ሲጠበቁ የነበሩት እና በአሁን ሰአት በሚኖሶታ የመጀመሪያውን ስብሰባቸውን ያደረጉት የሰማያዊ ፓርቲ አመራር (ሊቀመንበር) የሆኑት ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት በነገው እለት በችካጎ ከተማ ደማቅ ስብሰባ እንደሚያካሂዱ ተጠቆመ ። በነገው እለት በሊዊስ ሚሞርያል ሆስፒታል አዳራሽ የሚከናወነው ስብሰባ በ፪፡00 ሰአት የሚጀመር ሲሆን ማንኛውም ኢትዮጵያዊ እና የኢትዮጵያዊነት ጉዳይ ያገባኛል የሚል ሁሉ ለዚህ ስብሰባ ተሳታፊ እንዲሆን አስተባባሪዎቹ ጥሪ አቅርበዋል ። የሰማያዊ ፓርቲ የመጀመሪያው የሆነው አለም አቀፍ የስብሰባ ጥሪ በሰሜን አሜሪካ በሚኒያፖሊስ ከመጀመሩም በላይ በስኬት መጠናቀቁን የዘሃበሻ አዘጋጆች ለማለዳ ታይምስ ዝግጅት ክፍል በላኩት መረጃ ገልጸዋል ። የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር የሆኑት ኢንጂነር ይልቃል ይህንንን የሰሜን አሚሪካ ጉⶋቸው የተደረገበት ዋነኛ ምክንያት ለመጭው ግንቦት ለሚካሄደው ስብሰባ የሚደረግ የገንዘብ ማሰባሰብ ሂደት ለማድረግ እና የፓርቲያቸውን ጥንካሬ በማሳየት እና በገው ፓርቲ የሚደርስባቸውን እንግልት እና እስር እንዲሆም ሞራላዊ እና ፖለቲካዊ ቀውስ ተቋቁመው የደረሱበትን ደረጃ ሊገልጹ የሚችሉበት መድረክ ማዘጋጀታቸውን የዚህ ስብሰባ አዘጋጆች ጠቁመዋል ። ኢ/ር ይልቃል በኢትዮጵያ የምርጫ ሂደት ምን ይመስላል፣ ምርጫው ውስጥ መቆየት ያለው ፋይዳ፣ የሰማያዊ ፓርቲ አጠቃላይ ገፅታና እንቅስቃሴ ምን ይመስላል፣ በሚሉት ጥያቄዎች ላይ ውይይት እንደሚያደርጉ ኮሚቴው ገልጿል፡፡

የፓርቲውን የሰላማዊ ትግል ስትራቴጂዎች በውጭ ሀገር ለሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን ማስረዳትና በነዚህ ጉዳዮች እንዲሁም ባጠቃላይ የአገራችን ወቅታዊ ሁኔታዎች ዙሪያ ከኢትዮጵያዊያን ጋር ዉይይት ማኪያሄድም የዝግጅቱ አንድ አካል መሆኑም በመግለጫው ተጠቅሷል።

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 9 years ago on April 18, 2015
  • By:
  • Last Modified: April 18, 2015 @ 8:28 pm
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar