www.maledatimes.com እነተስፋለም ወልደየስ ተፈቱምክንያቱ የፕረዚዳንት ባራክ ኦባማ ወደ ኢትዮጵያ የጉዞ እቅድ ነው ተባለ - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

እነተስፋለም ወልደየስ ተፈቱምክንያቱ የፕረዚዳንት ባራክ ኦባማ ወደ ኢትዮጵያ የጉዞ እቅድ ነው ተባለ

By   /   July 8, 2015  /   Comments Off on እነተስፋለም ወልደየስ ተፈቱምክንያቱ የፕረዚዳንት ባራክ ኦባማ ወደ ኢትዮጵያ የጉዞ እቅድ ነው ተባለ

    Print       Email
0 0
Read Time:1 Minute, 31 Second

safe_image278LG8IB_tesefalem1Zelalem_zone9_1

ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ ፣ጋዜጠኛ አስማማው ሃይለጊዮርጊስ፣ ጦማሪ ዘላለም ክብረት፣ማህሌት ፋንታሁንና ጋዜጠኛ ኤዶም ካሳዬ ዛሬ ማምሳውን በፍትሕ ሚኒስቴር ውሳኔ መፈታታቸው የታወቀ ሲሆን ከቤተሰብ መቀላቀላቸው ከአዲስ አበባ የወጡ መረጃዎች ገለጹ።የቀሩት በእስርና በስደት ያሉ አምስት ጦማሪያን ጉዳኢ በተጀመረው የክስ ሂደት ይቀጥላል ቢባልም ቁርጥ አለ ውሳኔ አለመሰጠቱ ታውቋል። በክሱ ላይ ብኢን ለመስጠት ከመጪው ቀጠሮ ሐምሌ 13 ቀን 2007 በፊት ይፈቱ ዌኢ እንደተባለው ክሱ ቀጥሎ ብይን ይሰጥ አልታወቀም።

ከአስሩ ጦማሪያንና ጋዜጠኞች መካከል የክስ ሂደታቸው ይቀጥላል የተባለው የክሱ መዝገብ በስሟ የተከፈተውን ሶሊያና ሽመልስ ፣ አቤል ዋበላ ሱጌቦ፣ ናትናኤል ፈለቀ፣ በፍቃዱ ሃይሉ እና አጥናፉ ብርሃኔ ጉዳይ መታየቱ እንደሚቀጥል ከፍርድ ቤቱ የተገኘ መረጃ አመልክቷል።

የፍትህ ሚኒስቴር የፌደራል ተቋማትን ስልጣን እና ተግባር ለመደንገግ በወጣው አዋጅ ቁጥር 691/2003 አንቀፅ 16 መሰረት በማናቸውም ሰዓት የተጀመረ ምርመራ እና ክስ የማቋረጥ እና የማንሳት ስልጣን እንዳለው ይታወቃል ያለው አንድ የአገዛዙ ሚዲአ ፍቺውን ሕጋዊ ላማድረግና በሕግ መሰረት የተሰራ ለማስመሰል ሞክሯል። በዚህ መዝገብ አቃቤ ህግ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ የወንጀል ችሎት ምስክሮችን ማሰማቱን ተከትሎ ችሎቱ ብይን ለመስጠት ለሀምሌ 13 ቀን 2007 መቅጠሩን አስቀድመን መዘገባችን ይታወሳል።

የዞን ዘጠኝ ጦማሪአንም ሆኑ ሌሎች በእስር ላይ ያሉ ጋዜጠኞችና የፖለቲካ መሪዎች በፈጠራ መንግስትን በሀይል ለመታልና በሽብር በሚል ተከሰው ያለ በቂ ማስረጃ በትዕዛዝ የተፈረደባቸውና ጉዳያቸውን እተከታቱ ያሉት መጨረሻ ለጊዜው ባይታወቅም የፕ/ት ኦባማ የኢትዮጵያን ጉዞ ዕቅድ በምሳሌነት የሚያነሱ መደመጥ ጀምረዋል።

ለአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ግልጽ ደብዳቤ የጻፈውን ጦማሪ ናትናኤል ፈለቀን ጨምሮ ክሳቸው ይቀጥላል የተባሉት አምስቱ ጦማሪያን ጉዳይ ከሐምሌ 13 ቀተሮ በፊት ይቋጭ ለጊዜው የታወቀ ነገር የለም።

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋን ጨምሮ በርካታ ጋዜጠኞች፣ የፖለቲካ ድርጅት በተለያየ ደረጋ ያሉ መሪዎች፣ የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላትና ሌሎችም ጉዳይ በተመለከተ አገዛዙ የሰጠው መግለቻ የለም።

 

ባለፈው ሰኔ 8/2007 ቀጠሮ አንደኛዋን ተከሳሽ ሲሊአና ሽመልስን ይመለከታል የተባለው <ሲ.ዲ >> በግልጽ ችሎት ይታያል ተብሎ ሲጠበቅ ዳኞች ያለ አንዳች ማብራሪያ በግልጽ ችሎት አይታይም በማስረጃነት ተቀብለነዋል ማለታቸው ይታወሳል።

የጦማሪያኑ መፈታት ከፕ/ት ኦባማ ጉዞ ጋር ይያያዝ ዌኢም በሌላ ምክንያት እስካሁን የሚታወቅ ባይኖርም አንዳንዶች የኦባማ ጉዞን እቅድ በምክንያትነት ያነሳሉ።

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 9 years ago on July 8, 2015
  • By:
  • Last Modified: July 8, 2015 @ 9:44 pm
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar