www.maledatimes.com የትህዴን መሪ አቶ ሞላ አስገዶም ትግሉን ትቶ ለምን ኮበለለ - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

የትህዴን መሪ አቶ ሞላ አስገዶም ትግሉን ትቶ ለምን ኮበለለ

By   /   September 15, 2015  /   Comments Off on የትህዴን መሪ አቶ ሞላ አስገዶም ትግሉን ትቶ ለምን ኮበለለ

    Print       Email
0 0
Read Time:1 Minute, 49 Second

ገዛኸኝ አበበ ከኖርዌይ

የትህዴን መሪ አቶ ሞላ አስገዶም ትግሉን ትቶ ለምን ኮበለለ ? ሊፈታ የሚገባ ጥያቄ የትህዴን መሪ አቶ ሞላ አስገዶም የተወሰኑ የትህዴን ሰራዊት ይዞ ሀገር ኢትዮጵያ ኮበለለ ይሄ ዜና ብዙዎቻችን እናዳስገረመ እና  አንዳንዶችንም እንዳሰደነገጠና፣ የተወሰኑ ግለሰቦችን እንደስደሰት እያየነው ያለ ነገርሲሆን የአቶ ሞላ  አስግዶም ከትግል ሜዳው መኮብለል እና ወደ ወያኔ ካምፕ መቀላቀል እኔን ባያስደነግጠኝ እና ባያስደስተኝም የአገር አድን ንቅናቄ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው በተሾሙ በማግስቱ ኮብልለው መጥፋታቸው   በጣም አገራሞትን ጭሮ ጥያቄ ስለፈጠረብኝ  ይችን ትንሽ ነገር ማለትን ወደድኩኝ:: በመጀመሪያ ልናውቀው የሚገባው ነገር እንደዚህ አይነት ነገር በትግል ውስጥ ሊያጋጥም እና ሊከሰት የሚችል እንደሆነ  መገንዘብ ያስፈልገናል::

እውነትና  ንጋትእያደር ይጠራል ቢሆንም ነገሩ እንደእኔ አመለካከት ግን አቶ ሞላ አስግዶም በመጀመሪያም ኤርትራ ተቀምጠው የየትግራይ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ እንቅስቃሴን (ትህዴን) በሊቀመንበርለ ሲመሩት የነበሩት በእርግጥ ጸረ ወያኔ አቋምና አላማ ኖሮቸው ነበር ወይስ ሌላ ስውርና የተደበቀ አጀናዳ በጉያቸው ደብቀው አስመሳይነትን ተላብሰው ውስጥ ውስጡን የየወያኔ ፖለቲካዊ አጀንዳ ሲያስፈጽሙ የነበሩ ሰው ነበሩ ወይ የሚለውን ነገር እንድጠረጥር ቢያደርጉኝም  ምንአልባትም ማን ያውቃል እኝህ ሰው የሆነ ጊዜያዊ ጥቅም መሻት አታሏቸው ይሆን የሚልም ነገር እንዳስብ አድርጎኛል:: ምክንያቱም ለእውነት እንዳንታገል ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል አንዱ ለጊዜያዊ  ጥቅም መታለል በመሆኑ። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንኮን ተዘግቦ እንደምናገኘው ኤሳው ለሆዱ ብሎ በምስር ወጥ ብኩርናውን አሳልፎ ለወንድሙ ለያዕቆብ እንደሸጠው ሁሉ ዛሬም በዚህ ዘመን ለጊዜያዊ ጥቅም ተብሎ ማንነትንና ሕሊናን በመሸጥ አስመሳይነትን ተላብሰው ለእውነት ከመቆም ይልቅ የተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞችን ተቀብለው ከእውነት ጋር የተጣሉ በርካቶች ሰዎች እንዳሉ እናውቃለን።

ሰው ለተለያዩ ጥቅሞች ሲል አስመሳይነትን ተላብሶ መኖርን የሚችል ፍጡር ነው::አስመሳይነት ዛሬ የጀመረ ብቻም ሳይሆን በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ አሉታዊ ተጽኖ ከፈጠሩ ጉዳዮች መካከል ትልቁን ስፍራ ይዞ እናገኘዋለን። በጥቅም ታውረው አስመሳይነትን ተላብሰው በጣሊያን ወረራ ዘመን መንገድ እየመሩ ወደ መሀል ሀገር ከማስገባት በተጨማሪም የንጉሠ ነገሥቱ የቅርብ ባልሙዋል ከነበሩ መኩዋንንቶች እና መሳፍንቶች መካከል ሳይቀሩ ለጣሊያን ያደሩ ሰዎችን እንደምሳሌ ማንሳት ይቻላል። እነዚህ በአስመሳይነት የተጠቁ ወገኖች ወይም ሹማምንቶች ህዝቡ ተቃውሞውን በማቆም መሰሪዋ ጣሊያን ይዛው የመጣችውን የይምሰል እውቀት እና ስልጣኔ በመቅሰም ሀገሩን ያለማ ዘንድ በሀሰት ለመሸንገል ሞክረዋል። መረጃ በመስጠት በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ደማቸው በግፍ እንዲፈስ ያደረጉት አስመሳዮች ወይም ጥቅመኞች ናቸው።

ዛሬም አስመሳይ ጥቅመኞች ጊዜያዊ ጥቅምን እና የወያኔን ትርፍራፊ ለመልቀም ቢኮበልሉ ድሩም ከትግል ጉራው የነበሩት  ታሪክን ለመበረዝ፣ የህዝብን ለመግደል ስለነበረ የሚያስደነግጥ ነገር አይኑርም ባይ ነኝ ምክንያቱም ነገም ሌላ ነገር ልንሰማ እንችል ይሆናልና ስለሆንም ማንኛችንም ከአስመሰይነት ተላቀን ማንነትንና ሕሊናን በጥቅም ሳንሸጥ እንደ ዜጋ ለሀገር በማሰብ ለነጻነት፣ ፍትህና ዲሞክራሲ በጽኑ መታገል ይኖርብናል በማለ  ዘመኑን የድል ያድርግልን እላለው።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!!

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 9 years ago on September 15, 2015
  • By:
  • Last Modified: September 15, 2015 @ 12:06 pm
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar