www.maledatimes.com በሕወሓት የሚመራው ድርጅት ላልሠራው ሥራ ክፍያ ተፈጸመለት - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

በሕወሓት የሚመራው ድርጅት ላልሠራው ሥራ ክፍያ ተፈጸመለት

By   /   June 16, 2017  /   Comments Off on በሕወሓት የሚመራው ድርጅት ላልሠራው ሥራ ክፍያ ተፈጸመለት

    Print       Email
0 0
Read Time:1 Minute, 18 Second

 

 

የህወሓት ባለስልጣናት በንግድ ስም ገንዘብ ለማጭበርበር ያቋቋሙት የብረታ ብረት እና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ)፣ ላልሰራው ስራ 3 ነጥብ 4 ቢሊዬን ብር ክፍያ እንዲፈጸምለት መጠየቁ ተነገረ፡፡ በህወሓት ወታደራዊ አዛዦች የሚመራው ይኸው የንግድ ተቋም፣ በሀገሪቱ የሚገኙ የፋብሪካ እና መሰል ፕሮጀክቶችን ያለ ተቀናቃኝ በመውሰድ የሚታወቅ ሲሆን፣ በዚህም የተነሳ የግል ባለሀብቱን ከገበያ ውጪ በማድረግ ብዙዎችን አማርሯል፡፡ ሜቴክ ለስም በመከላከያ ሚኒስቴር ስር ይቋቋም እንጂ፣ የሚዘውሩትም ሆነ ገንዘቡን የሚረጩት የህወሓት ባለስልጣናት ናቸው፡፡

ከዚህ ቀደም ያዩ የተባለውን እና በኦሮሚያ ክልል የሚገኘውን የማዳበሪያ ፋብሪካ ለመገንባት ኮንትራቱን የወሰደው ሜቴክ፣ ግንባታውን እጅግ ከማዘግየቱም በላይ ገና ስራውን ሳይጨርስ ተጨማሪ ክፍያ እንዲሰጠው ጠይቋል፡፡ ከተጨማሪ ክፍያው በላይ ደግሞ፣ 40 በመቶ ብቻ ላጠናቀቀው የፋሪካው ስራ 60 በመቶ የሚሆነውን ከፍያ መውሰዱም ተነግሯል፡፡ በአንድ የቻይና ድርጅት በተደረገው ጥናት መሰረት፣ የስኳር ፋበሪካውን ገንብቶ ለመጨረስ አራት ዓመት ብቻ እንደሚፈጅ ተነግሮ ነበር፡፡ ሆኖም ሜቴክ በፋብሪካው ላይ የተደረገውን ጥናት በድጋሚ በመከለስ፣ የፋብሪካውን ግንባታ በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ አጠናቅቀዋለሁ ብሎ ዝቶ ነበር፡፡ በዚህም መሰረት ኮንትራቱ የተሰጠው ሜቴክ፣ ግንባታውን በ2004 ጀምሮ በ2006 እንደሚያተናቅቀው ገልጾ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ላይ የፋብሪካው ስራ የተጠናቀቀው ግን 40 በመቶዉ ብቻ ሆኖ ተገኝቷል፡፡

የፋብሪካው ስራ ገና አርባ በመቶ ላይ በሚገኝበት ሁኔታ በህወሓት የሚመራው ሜቴክ ግን ከአጠቃላይ የፕሮጀክቱ የውል ዋጋ ብር 11,084,850,000.00 (አስራ አንድ ቢሊየን ሰማንያ አራት ሚሊየን አምስት መቶ ሺ ብር) ውስጥ ብር 5,653,273,500.00 (አምስት ቢሊየን 653 ሚሊየን 273 ሺ 500 ብር) ወይም የውሉ 60 በመቶ ከፍያ ተፈጽሞለታል፡፡ ድርጅቱ ፋብሪካውን ገንብቶ ለማጠናቀቅ የገባውን ቃል ከማጠፉም በላይ፣ ያልሰራበትን ክፍያ ጭምር መውሰዱ፣ ህወሓት በስርዓቱ ውስጥ ያለውን የበላይነት እንደሚያረጋግጥ ታዛቢዎች ይናገራሉ፡፡ የህወሓት ባለስልጣናት በቀጥታ ከሚዘርፉት የሀገር ሀብት በተጨማሪ፣ በንግድ ስም ደግሞ በሜቴክ በኩል ከፍተኛ ገንዘብ በማሸሽ ላይ መሆናቸውን መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 7 years ago on June 16, 2017
  • By:
  • Last Modified: June 16, 2017 @ 10:08 am
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar