www.maledatimes.com በሲያትል የኢትዮጵያዊው አሟሟት እንቆቅልሽ አልተፈታም - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

በሲያትል የኢትዮጵያዊው አሟሟት እንቆቅልሽ አልተፈታም

By   /   July 26, 2017  /   Comments Off on በሲያትል የኢትዮጵያዊው አሟሟት እንቆቅልሽ አልተፈታም

    Print       Email
0 0
Read Time:50 Second

 


አድማስ ዜና፦ ከሲያትል የተሰማው ዜና አሳዛኝ ነው። ባለፈው እሁድ፣ ጁላይ 23 ንጋት ላይ ነው፣ የ 36 ዓመቱ ይትባረክ ደሞዝ፣ ለባለቤቱ፣ “ጓደኞቼን አንድ ቦታ ማድረስ አለብኝ” ይላትና ይወጣል። በምን ምክንያት እንደሆነ አይታወቅም፣ የጠቀሳቸው ሰዎችና እሱ፣ 25 ጫማ ርዝመት ባለው የይትባረክ ጀልባ ላይ ተሳፍረው ዩኒየን በተባለ ሐይቅ ላይ ነበሩ።

በመካከል ድንገት ለፖሊስ አንድ ጥሪ ይደርሳል፣ ጥሪውም ከንጋቱ 7 ሰአት አካባቢ ሲሆን፣ በዚህ በዩኒየን ሐይቅ አካባቢ ከሚገኝ ጀልባ አካባቢ ጩኸትና ግርግር ይሰማል የሚል ነበር። ፖሊስ ከስፍራው ሲደርስ፣ በርካታ ሰዎች ጀልባው ላይ ነበሩ፣ እየተጯጯሁም ከመካከላቸው አንዱ ሐይቁ ውስጥ መግባቱንና ሳይወጣ መቅረቱን ይናገራሉ። ፖሊስም ልዩ መሳሪያ በመጠቀም ገባ የተባለውን ሰው ፣ ህይወቱ አልፎ ሊያገኘው ችሏል። ያ ሰው ይትባረክ ደሞዝ ነበር።

ይትባረክ ደሞዝ የሲያትል ከተማ የረዥም ጊዜ ነዋሪ ሲሆን፣ በትራክ ኩባንያ ለረዥም ጊዜ ሰርቷል። የሁለት ልጆች አባትም ነው። በቅርብ የሚያውቁት ሁሉ አሟሟቱ እንቆቅልሽ እንደሆነባቸው ይናገራሉ። ፖሊስ አስከሬኑን እየመረመርኩ ነው፣ የምርመራውን ውጤትም በቅርቡ አሳውቃለሁ ብሏል። ዘልሎ ገብቶ ይሁን ሆን ተብሎ፣ ወይም ሌላ ምክንያት ይኑር ከምርመራው በኋላ የሚታወቅ ይሆናል። አድማስ ሬዲዮ በቅዳሜ ፕሮግራሙ የምርመራውን ውጤት ጨምሮ የሚያውቁትንም ሰዎች በማነጋገር ተጨማሪ መረጃ ይዞ ለመቅረብ ይሞክራል።

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 7 years ago on July 26, 2017
  • By:
  • Last Modified: July 26, 2017 @ 10:13 am
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar