Read Time:30 Second
የአዲስ አበባ ፖሊስ⬇️
በአዲስ ዓመት ዋዜማ በአዲስ አበባ ከተማ በደረሰ የትራፊክ #አደጋ የ3 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ በ6 ሰዎች ላይ ደግሞ #ከባድ እና #ቀላል የመቁሰል አደጋ መድረሱን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ገለፀ፡፡
የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ ኢንስፔክተር ማርቆስ ታደሰ በተለይ ለኢቲቪ በስልክ እንደገለፁት አደጋዎቹ የደረሱት በአቃቂ፣ ቦሌ እና የካ ክፍለ ከተሞች ነው፡፡
አደጋዎቹ የደረሱት እግረኞች መንገድ በማቋረጥ ላይ ባሉበት ወቅት መሆኑን የገለፁት ባለሙያው የአደጋው መንስኤ እየተጣራ ነው ብለዋል፡፡
በሌላ በኩል የእሳትና ድንገተኛ አደጋዎች መከላከል እና መቆጣጠር ባለሥልጣን በዋዜማውም ሆነ በዛሬው ዕለት ምንም አይነት የእሳት አደጋ #አለመከሰቱን ገልጿል፡፡
በአዲሱ ዓመት ሕብረተሰቡ ከተለያዩ አደጋዎች እራሱን እንዲጠብቅና ጥንቃቄ እንዲያደርግ መስሪያ ቤቶቹ አሳስበዋል።
©etv
Wondering where the comments are? We encourage you to use the share buttons below and start the conversation on your own!
- Email a link to a friend (Opens in new window) Email
- Share on Facebook (Opens in new window) Facebook
- Share on X (Opens in new window) X
- Share on LinkedIn (Opens in new window) LinkedIn
- Share on Pinterest (Opens in new window) Pinterest
- Share on Tumblr (Opens in new window) Tumblr
- Print (Opens in new window) Print



Print
Email
Average Rating