www.maledatimes.com ከህወሃት የጽንፈኛ መንግስት በከፍተኛ ወንጀል ክስ ከሚጠረጠሩት መካከል የደህንነት ሚንስትሩ ጌታቸው አሰፋ ወደ አሜሪካ እንዳይገባ የሚያግድ ትእዛዝ ተላለፈበት - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Addis Admas  >  Current Article

ከህወሃት የጽንፈኛ መንግስት በከፍተኛ ወንጀል ክስ ከሚጠረጠሩት መካከል የደህንነት ሚንስትሩ ጌታቸው አሰፋ ወደ አሜሪካ እንዳይገባ የሚያግድ ትእዛዝ ተላለፈበት

By   /   November 26, 2018  /   Comments Off on ከህወሃት የጽንፈኛ መንግስት በከፍተኛ ወንጀል ክስ ከሚጠረጠሩት መካከል የደህንነት ሚንስትሩ ጌታቸው አሰፋ ወደ አሜሪካ እንዳይገባ የሚያግድ ትእዛዝ ተላለፈበት

    Print       Email
0 0
Read Time:1 Minute, 40 Second

ከህግ ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ከተላለፈ ደብዳቤ እንደሚያመለክተው ከሆነ የህወሃት ጽንፈኛ እና ዘራፊ ቡድን ከነበረው የደህንነት አባል እንዲሁም ህዝብን በማፈን እና በመጨቆን ለሃሳባት አመታት በዜጎች ላይ ከፍተኛ በደል አድርሷል ተብሎ ከፍተኛ ክስ የቀረበበት እና በአሁን ሰአት በመቀሌ ከታመ መሽጎ የሚገኛው የቀድሞው የደህንነት ሹም በየትኛውም አቅጣጫ ወደ አሜሪካ እንዳይገባ የሚል ማዘዣ እንደወጣበት ተገልጿል ። በሌላም በኩል ለአውሮጳ ህብረትም ተመሳሳይ ደብዳቤ መጻፉን የሚጠቁሙ ምንጮች አሉ።

በአለም አቀፍ የወንጀል ክስ ይከሰሳሉ ተብለው ከሚጠበቁት የህወሃት ግንባር ቀደም ወንጀለኞች መካከል የደህንነት ሚንስትሩ አቶ ጌታቸው አሰፋ እንደሆኑ የሚታወቅ ነው ። አቶ ጌታቸው አሰፋ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ፎⶆቸውን እንኳን በአግባቡ የሚያውቅ ያለነበር ሲሆን የፋና ቴሌቪዥን በስህተት በስብሰባ ላይ በነበሩበት ወቅት ለማሳየት መሞከሩ የሚታወስ ሲሆን እርሳቸውን የሚያውቁ እና በእርሳቸው ስር ከፍተኛ ድብብደባ እና በደል የደረሰባቸው ጋዜጠኞች ማንነታቸውን በፌስቡክ እና በዌብሳይቶቻቸው ሳይቀር ከቴሌቪዥኑ ስርጭት በኋላ ሲያጋሩ መክረማቸው ይታወሳል ፡፤ የእኝህን ወንጀለኛ ጥልቅ መረጃ የአሜሪካ ኤምባሲም የወንጀለኛ ምርመራ ቡድን ጋር በጥምረት ማጥናታቸውን እና ለፍርድ መቅረብ የሚቻልበትን መንገድ ማመቻቸት እንደሚችሉ ምንጮች ይጠቁማሉ። ከሰሞኑ በመቀሌ እና አካባቢዋ በተደረገ ሰልፍ ምክንያት አብዛኛውን የኢትዮጵያን ማህበረሰብ ያስቆጣ ከመሆኑም በላይ ለትግል ተነስተናል ማለታቸው እና ለ፳፯ አመታት ኢትዮጵያ የነጻነትን ጥያቄ ሲያቀርቡ ምንም አይነት ድምጸትን ያላሰሙት እነዚሁ ወገኖች ዛሬ በሌብነት ተጠርጥረው ወደ ዘብጥያ ለወረዱ ባለስልጣናት ሰላማዊ ሰልፍ መውጣታቸው …ከኢትዮጵያ ሌብነትን የሚያበረታቱ ዜጎች በሚል ቅጽል ስም እየተሰጣቸው ከፍተኛ ውግዘት በሶሻል ሚዲያ ሲተላለፍባቸው መስተዋላችን ይታወቃል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ለህዝብ እና ለሃገር እኩልነት በህግ እና በስርአት የህወሃት አስተዳደር ባወጣው የህግ አዋጅ መሰረት ተገቢውን አሰራር በመጠቀም ማንኛውም ወንጀለኛ ባጠፋው ጥፋት መሰረት ተገቢውን እርምጃ ቢወሰድበት ተቀባይነት ሊኖረው እንደሚችል የትግራይ ሰዎች ቢያገናዝቡት ጥሩ ነበር ያሉ አንዳንድ ግለሰቦች እንዳሉ አይጠፋም።

ማለዳ መረጃ ማእከል

The U.S. Department of State responded to Honorable Congressman Mike Coffman ‘s letter to apply the Global Magnistky Act be imposed against Former Ethiopian National Intelligence and security chief Getachew Assefa.
It is a subsequent step to #Hr128, using the Global Magnitsky Act. The sanction will freeze assets in the United State that belong to Getachew Assefa, he will also be unable to get a visa to the US. The sanction could also include the European Union and partner countries.

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

♦ “ ትክክለኛ ፍትሕ አይሰጡም” የተባሉት የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛ ከችሎት እንዲነሱ ተጠየቀ !

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar