Read Time:35 Second

አዲስ ማለዳhttp://WWW.MALEDATIMES.Com
ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የኅብረተሰቡን ተደራሽነትን ለማስፋት አዲስ መተግበሪያን ዓርብ፣ ታኅሣሠ 19 ይፋ አደረገ።
አዲሱ የመረጃ ቋትን የያዘው መተግበሪያ በሕግና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ መረጃዎችን ለማግኘት ጉልህ አስተዋፅኦ ያደርጋል የሚል ተስፋም ተጥሎበታል። መተግበሪያው ከ1934 እስከ 2010 ድረስ ያሉ ሕጎችን፣ አዋጆችን፣ ደንቦችንና የሰበር ውሳኔዎችን አካቶ የያዘ የመረጃ ቋት ነው ተብሏል። ይህ መተግበሪያ የበይነ መረብ አገልግሎት በማይገኝባቸው ቦታዎችም ለተጠቃሚዎች መረጃ ማግኘት የሚያስችል መሆኑም ተነግሮለታል።
የመረጃ ቋት መተግበሪያውን ተንቀሳቃሽ ስልኮችን ጨምሮ በሌሎች የኤሌክትሮኒክስ መሣሪያዎች ላይ በመጫን መጠቀም ይቻላል። መተግበሪያው የተለያዩ ሕጎች ሲሻሻሉም በራሱ ጊዜ የመረጃ ቋቱን እንደሚያሻሽልና በአዲስ እየተካ እንደሚሄድ ተነግሮለታል።
ጠቅላይ ዐቃቤ ሕጉ ብርሃኑ ጸጋዬ እንዳሉት የአሠራር ሒደቱን ለማዘመን በማሰብ የቀረበው መተግበሪያ ኢትዮጵያ ለ53 ዓመታት የነበሯትን የተለያዩ የሕግ ማዕቀፍ ሰነዶች ለተጠቃሚዎች በቀላሉ እንዲደርሱ የሚረዳ ነው።
Wondering where the comments are? We encourage you to use the share buttons below and start the conversation on your own!
- Email a link to a friend (Opens in new window) Email
- Share on Facebook (Opens in new window) Facebook
- Share on X (Opens in new window) X
- Share on LinkedIn (Opens in new window) LinkedIn
- Share on Pinterest (Opens in new window) Pinterest
- Share on Tumblr (Opens in new window) Tumblr
- Print (Opens in new window) Print



Print
Email
Average Rating