Read Time:25 Second
የአለም ምግብ ፕሮግራም አዳማ ከሚገኘው መጋዘኑ ሱማሌ ክልል ዳዋ ዞን፣ ለሚገኙ ተረጂዎች መድረስ የነበረበት 436 ቶን የምግብ ውጤቶች በአካባቢው አለመረጋጋት ምክንያት ማድረስ አለመቻሉን ገለጸ።
የምግብ ውጤቶቹን የያዙት 10 ተሸከርካሪዎች ከአዳማ በመነሳት በነገሌ ወረዳ በኩል ቢንቀንሳቀሱም በዳዋ ዞን አጎራባች አካባቢዎች ባለው ብጥብጥ የተነሳ ወደ ተረጂዎች መድረስ አልቻሉም።
በዚህም ተሽከርካሪዎቹ የያዙትን ምግብ ሌሎች በሱማሌ ክልል ወደሚገኙ ተፈናቃዮች ወስዶ ለማራገፍ መገደዱን አሳውቋል።
ወደ 350 ሺህ የሚጠጉ ተፈናቃዮች በዳዋ ዞን ዕርዳታውን እንደሚጠብቁ ያሳወቀው ድርጅቱ፣ በአካባቢው ባለው አለመረጋጋትና ከመንገዱ መፈራረስ ጋር ተያይዞ ስራውን በአግባቡ መወጣት አለመቻሉንም ገልጿል።
Wondering where the comments are? We encourage you to use the share buttons below and start the conversation on your own!
- Email a link to a friend (Opens in new window) Email
- Share on Facebook (Opens in new window) Facebook
- Share on X (Opens in new window) X
- Share on LinkedIn (Opens in new window) LinkedIn
- Share on Pinterest (Opens in new window) Pinterest
- Share on Tumblr (Opens in new window) Tumblr
- Print (Opens in new window) Print



Print
Email
Average Rating