www.maledatimes.com የቀድሞ የሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት አብረዋቸው የታሰሩ ተከሳሾች በዓቃቤ ሕግ ላይ ተቃውሞአቸውን አሰሙ - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

የቀድሞ የሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት አብረዋቸው የታሰሩ ተከሳሾች በዓቃቤ ሕግ ላይ ተቃውሞአቸውን አሰሙ

By   /   March 31, 2019  /   Comments Off on የቀድሞ የሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት አብረዋቸው የታሰሩ ተከሳሾች በዓቃቤ ሕግ ላይ ተቃውሞአቸውን አሰሙ

    Print       Email
0 0
Read Time:1 Minute, 47 Second

የቀድሞ የሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት አብረዋቸው የታሰሩ ተከሳሾች በዓቃቤ ሕግ ላይ ተቃውሞአቸውን አሰሙ
የሶማሌ ክልል የቀድሞ ፕሬዚዳንት አቶ አብዲ መሐመድ

በሶማሌ ክልል በጅግጅጋ ከተማና በሌሎች የክልሉ ከተሞች በደረሱ የጅምላ ግድያ፣ አካል ማጉደል፣ አስገድዶ መድፈር፣ በዘር ለይቶ ማጥቃት፣ የሃይማኖት ተቋማት ቃጠሎ፣ ንብረት ማውደምና ሌሎች የወንጀል ድርጊቶች ክስ የተመሠረተባቸው የክልሉ የቀድሞ ፕሬዚዳንትን ጨምሮ በእስር ላይ የሚገኙት ተከሳሾች፣ በዓቃቤ ሕግ ላይ ተቃውሞአቸውን አሰሙ፡፡

ተከሳሾቹ ዓርብ መጋቢት 20 ቀን 2011 ዓ.ም. ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አራተኛ ወንጀል ችሎት ተቃውሞአቸውን ያሰሙት፣ እነሱ በእስር ላይ መሆናቸውን እያወቀ በፌዴራል ፖሊስ በኩል መቅረብ ያለባቸውን ተከሳሾች በሚመለከት ተከታትሎ በምን ደረጃ ላይ እንዳለ ለፍርድ ቤቱ መግለጽ ሲገባው፣ ከተከሳሾች እኩል የፌዴራል ፖሊስ ያቀረበውን ምላሽ መስማቱን በሚመለከት ነው፡፡

የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ ክስ ከመሠረተባቸው 47 ተከሳሾች መካከል አቶ አብዲ መሐመድ፣ ወ/ሮ ራሀማ መሐመድ፣ አቶ አብዱረዛቅ ሳኒና አቶ ፈራሃን ጣሂርን ጨምሮ ስድስት ሲሆኑ፣ ቀሪዎቹን 41 ተከሳሾች የፌዴራል ፖሊስ በአድራሻቸው አፈላልጎ እንዲያቀርብ ትዕዛዝ ተሰጥቶት ነበር፡፡ ነገር ግን የፌዴራል ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ መጋቢት 20 ቀን 2011 ዓ.ም. በላከው ደብዳቤ ተከሳሾቹን አፈላልጎ ለማቅረብ አለመቻሉን ገልጾ፣ በአድራሻቸው ተከታትሎና አፈላልጎ ለማቅረብ ረዘም ያለ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል፡፡

ዓቃቤ ሕግ በበኩሉ ለፍርድ ቤቱ እንደገለጸው፣ ፌዴራል ፖሊስ የት ሄዶና አፈላልጎ እንዳጣቸው አለመግለጹ በትጋት አለመሥራቱን አያመለክትም፡፡ በቀጣይ ቀጠሮ የት ቦታ ሄዶ እንደፈለገና እንዳጣቸው ማረጋገጫ ከክልሉ ይዞ እንዲቀርብ ለፍርድ ቤቱ አመልክቷል፡፡ የክልሉ ፖሊስም እንዲተባበርና ተፈላጊዎቹን አፈላልጎ በመያዝ አብሮ እንዲሠራ ትዕዛዝ እንዲሰጥለትም ጠይቋል፡፡

የፌዴራል ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ የጻፈውን ደብዳቤና ዓቃቤ ሕግ ለፍርድ ቤቱ የሰጠውን አስተያየት የሰሙት የተከሳሾች ጠበቆች፣ አስተያየት መስጠት የጀመሩት በተቃውሞ ነው፡፡ ፍርድ ቤቱ ቀደም ባለው ችሎት ትዕዛዝ ሲሰጥ በትጋት ሠርቶ እንዲያቀርብ ጥብቅ ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው ማመልከታቸውን አስታውሰው፣ ያ ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው ያሳሰቡት ምላሹ አሁን የተሰማው እንደሚሆን በመገመታቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ጠበቆቹ ዓቃቤ ሕግ የፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ የት እንደደረሰና ምን ውጤት እንደተገኘ በስልክና በአካል በመገኘት ማወቅ ሲገባው፣ እንደ ተከሳሽ እኩል በችሎት አስተያየት መስጠቱና የፖሊስን ሥራ መቃወሙ አስገራሚ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ተገቢም እንዳልሆነም አክለዋል፡፡ ደንበኞቻቸው ለረጅም ጊዜያት በእስር ላይ በመሆናቸው የዓቃቤ ሕግ ተጨማሪ የማፈላለጊያ ጥያቄ ውድቅ ተደርጎ፣ ያልቀረቡት ተከሳሾች በጋዜጣ እንዲጠሩ ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው ጠይቀዋል፡፡

የግራ ቀኙን ክርክር የሰማው ፍርድ ቤቱ፣ ዓቃቤ ሕግ የሰጠው አስተያየትና ያቀረበው ጥያቄ ተገቢነት የሌለው መሆኑንና እንዳልተቀበለው በመግለጽ፣ ሥራውን የራሱ አድርጎ መከታተል እንዳለበት አስታውቋል፡፡ በሌላ በኩል ፖሊስ ያለው በተሰጠው አድራሻ ተከሳሾችን ሊያገኛቸው ባለመቻሉ በቂ ጊዜ ተሰጥቶት አፈላልጎ እንዲያቀርብ በመሆኑ፣ በቀጣይ በትጋትና ከክልሉ ፖሊስ ጋር በትብብር በመሥራት፣ የደረሰበትን ውጤት በማስረጃ ጭምር እንዲያቀርብ በማሳሰብ ለሚያዝያ 24 ቀን 2011 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 5 years ago on March 31, 2019
  • By:
  • Last Modified: March 31, 2019 @ 3:13 pm
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar