www.maledatimes.com የኮንስትራክሽን ኩባኒያው በ51 ሚሊዮን ብር የግብር ስወራ ተከሰሰ - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

የኮንስትራክሽን ኩባኒያው በ51 ሚሊዮን ብር የግብር ስወራ ተከሰሰ

By   /   August 5, 2019  /   Comments Off on የኮንስትራክሽን ኩባኒያው በ51 ሚሊዮን ብር የግብር ስወራ ተከሰሰ

    Print       Email
0 0
Read Time:57 Second

Maleda News

ፓወር ኮን የግንባታ ተቋራጭ ድርጀት ለመንግሥት መክፈል የነበረበትን 51 ሚሊዮን ብር ግብር ሰውሯል በሚል በፌደራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ንግድ ችሎት ክስ ተመሰረተበት።

በድርጅቱ ግብይት ላይ ከ2006 ጀምሮ በተሠራ የምርመራ ኦዲት 25 የሚሆኑ ሐሰተኛ ደረሰኞችን ተጠቅሟል በሚል በግብር ስወራ ክስ ዐቃቤ ሕግክሱን መስርቷል። በሁሉም የግብር ዓይነቶች መንግሥት ማግኘት የነበረበትን ገቢ ሰውሯል በሚል በድርጅቱ ላይ በሰኔ ወር መጨረሻ ክስ መመስረቱንም ለማወቅ ተችሏል።

የኮንስትራክሽን ዘርፉን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች ላይ እየታየ ያለው የሐሰተኛ ደረሰኝ አጠቃቀም እየጨመረ መምጣቱን የገቢዎች ሚኒስቴር መግለጹ ይታወቃል።

በሚኒስቴሩ ፈቃድ የወጡ የሺያጭ መመዝገቢያ ማሽኖችን ለሕገወጥ ዓላማ በመጠቀም ሐሰተኛ ሰነዶችን በማተም የሚደረጉ ግብይቶች እየተንሰራፉ የመጡ መምጣታቸውን እና ደረሰኞቹን ወደ ገበያ የሚያስገቡ ግለሰቦች ላይ እርምጃ መውሰድ መጀመሩን ሚኒስቴሯ የኮንስተራክሽን ድርጅቶች በበኩላቸው የግብዓት በሚቀርቡላቸው ወቅት የሚያቀርቡት ግለሰቦች ሐሰተኛ ደረሰኞችን እንደሚያቀርቡላቸው እና ከመመሳሰላቸው የተነሳ እንደሚቸገሩ ይገልፃሉ።

ከግንባታ ሥራው ባሕሪ ጋር በተያየዘም የተለያዩ ግብዓቶች ወደ ግንባታ ቦታቸው በሚቀርቡ ጊዜ ደረሰኞችም እንደሚመጡ እና ይህም ለችግር እንዳጋለጣቸው ሲናገሩ ይደመጣሉ። በተለይም የሺያጭ መመዝገቢያ መሣሪዎች ከመሰወራቸው ጋር ተያይዞ በሕጋዊ መልኩ በወጡ መሣሪዎች ሐሰተኛ ግብይቶች መፈፀማቸው ራስ ምታት እንደሆኑበት ሚኒስቴሩ ሲገልፅ ቆይቷል።

በተጨማሪም ማንኛውም ግብይት ድርጅቱ በተመዘገበበት አድራሻ መደረግ እንዳለበት እና የጠፉ እንዲሁም ሕገወጥ ድርጊት እየተፈፀመባቸው ያሉ ማሽኖችን ዝርዝር በማውጣት በማስጠንቀቅ ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል።

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 5 years ago on August 5, 2019
  • By:
  • Last Modified: August 5, 2019 @ 8:54 am
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar