www.maledatimes.com ከአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ወደ አዲስ አበባ ከተማ የሚሄዱ ተጓዦች ለእንግልት እየተዳረጉ መሆናቸውን አስታውቀዋል! - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

ከአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ወደ አዲስ አበባ ከተማ የሚሄዱ ተጓዦች ለእንግልት እየተዳረጉ መሆናቸውን አስታውቀዋል!

By   /   October 11, 2019  /   Comments Off on ከአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ወደ አዲስ አበባ ከተማ የሚሄዱ ተጓዦች ለእንግልት እየተዳረጉ መሆናቸውን አስታውቀዋል!

    Print       Email
0 0
Read Time:55 Second

⬆️

Photo Maleda library

በደጀን እና ጎሃ ፅዮን መሥመር ወደ አዲስ አበባ ተጓዦችን አሳፍረው ሲሄዱ የነበሩ ተሽከርካሪዎች ወደ መጡበት እንዲመለሱ መደረጉንም የዓይን እማኞች ለአብመድ በስልክ ተናግረዋል፡፡

ተጓዦቹ ከረፋዱ 3:00 ገደማ ጀምሮ በጎሃ ፅዮንና አካባቢው እንዳያልፉ ተደርገዋል፡፡ ከ60 በላይ ተሽከርካሪዎችም ወደ ደጀን ከተማ እንዲመለሱ መደረጋቸውን ነው ያስረዱት፡፡

ክልከላው ‹‹በመጭው እሑድ አዲስ አበባ ላይ በተጠራው ሰልፍ ልትሳተፉ ነው›› በሚል እንደሆነም ነው ተጓዦች የጠቆሙት፡፡ ለአብመድ አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል በአማራ ክልል የሚገኙ መንፈሳዊ ቦታዎችን ጎብኝተው ወደ አዲስ አበባ በመመለስ ላይ የነበሩም ይገኙበታል፡፡ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚሔዱ ተማሪዎች እና ለሕክምና ክትትል ቀጠሮ ወደ አዲስ አበባ የሚሂዱ ተጓዦችም እንደንዳሉ ታውቋል፡፡ ጉዳዩ የሚመለከተው የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ከአዲስ አበባ ወደ አማራ ክልል የሚገቡ ተሽከርካሪዎች በሠላም እንዲገቡ እየተደረገ መሆኑን አስታውቋል፡፡

ከአማራ ክልል ወደ አዲስ አበባ እየሄዱ የነበሩ ተጓዦች ግን እንዳያልፉ መደረጉንና ወደ ደጀን እየተመለሱ መሆኑንም ኮሚሽኑ ከተሳፋሪዎች አገኘሁት ባለው መረጃ አረጋግጧል፡፡ የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ኮማንድ ፖስት ይህ ዜና እስከተጠናከረበት ጊዜ ድረስ የተጣራ መረጃ እንዳልደረሰው አስረድቷል፡፡

ከአስተያየት ሰጭዎቹ ያገኘነው መረጃ የሚያሳየው ግን ከረፋዱ 3:00 ጀምሮ ችግሩ እንደተፈጠረ ነው የተናገሩት፡፡ ኮማንድ ፖስቱ ጉዳዩን ለማጣራትም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየሠራ መሆኑን አስረድቷል፡፡

የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ መረጃው እንደደረሰው ገልጾ ዝርዝር ምክንያቱን እያጣራ እንደሆነ አስታውቋል፡፡

Source አብመድ

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 5 years ago on October 11, 2019
  • By:
  • Last Modified: October 11, 2019 @ 12:03 pm
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar