www.maledatimes.com ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተሰጠ መግለጫ - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተሰጠ መግለጫ

By   /   February 28, 2020  /   Comments Off on ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተሰጠ መግለጫ

    Print       Email
0 0
Read Time:51 Second

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፀረ-ፕላጃሪዝም (Anti-Plagiarism) ፖሊሲ ከየካቲት 22/2012 ዓ.ም ጀምሮ ሊተገብር መሆኑን በይፋ እየገለጸ ይህ ፖሊሲ ተግባራዊ የሚሆን ሲሆን በፖሊሲው መሰረት ከዚህ በኋላ ማንኛውም መመረቂያ ጽሁፍ (Thesis/Dissertation) በኧርከንድ (URKUND) ሶፍትዌር አማካኝነት ተመርምሮ ከፕላጃሪዝም ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥ ዲግሪ እንደማይሰጥ ያሳውቃል፡፡

ፕላጃሪዝም አንድ የምረቃ ፅሁፍ የሚያዘጋጅ ወይም የምርምር ስራ የሚሰራ ሰው ሌሎች ሰዎች የሰሩትን ስራ የራሱ እንደሆነ አድርጎ በመውሰድ የአካዳሚክ እና የምርምር ሕግጋትን በመጣስ የሚፈፅመው ሕገወጥ ተግባር ነው፡፡

ፕላጃሪዝም ተማሪዎች የመመረቂያ ጽሁፍ በሚያዘጋጁበት ጊዜ በራሳቸው ጥረት እና ልፋት የራሳቸው የሆነ (original) ስራ ሰርተው እንዳያቀርቡ በማድረግ ዩኒቨርሲቲው ጥራትን ለማረጋገጥ በሚያደርገው ጥረት ላይ ትልቅ ጉዳት ሲያደርግ የቆየ ሕገወጥ ተግባር ነው፡፡ ቀደም ሲል የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ፕላጃሪዝም በመጠቀም የመመረቂያ ጽሁፉን በማዘጋጀት 2ኛ ዲግሪ ወስዶ ከነበረ ተማሪ ላይ ድርጊቱ በማስረጃ በማረጋገጡ በሴኔት ሕጉ መሰረት ዲግሪው እንዲነጠቅ አድርጓል፡፡ ስለሆነም ዩኒቨርሲቲው ይህ ችግር በመማር ማስተማሩና በምርምር ስራ ላይ በየጊዜው እያስከተለ ያለው አሉታዊ ተፅእኖ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን በመገንዘቡ የፀረ-ፕላጃሪዝም ፖሊሲ ማውጣት አስፈላጊ ሆኖ አግኝቶታል፡፡ በመሆኑም ይህ ፖሊሲ ተግባራዊ ሲሆን ችግሩ ከሞላ ጎደል ይቃለላል የሚል ሙሉ እምነት አለው፡፡

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 4 years ago on February 28, 2020
  • By:
  • Last Modified: February 28, 2020 @ 3:34 pm
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar