ባለፈው አመት በእሬቻ በአል ህይወታቸውን ያጡ ወገኖች በአረብ ሀገራት ያሉ ኢትዮጵያውያኖች ሀዘኑን በጥልቅ በማሰብ አሳለፉ ፎቶዎችን ይዘናል ።
♥♥o
Read More →በእሬቻ በአል ሚስቴን ሲፈን ለገሰን ከነጠቁኝ በኃላ በኑሮዬም ሰላምን አሳጥተው ይከታተሉኛል (በእሬቻ በአል ተጎጂ ከሆነው አብዲሳ የተገለፀ)
https://m.youtube.com/watch?v=Gz1YbzZYCJM
Read More →ወያኔ ሌባ ነው ወያኔ ገዳይ ነው የሚሉ ጩኸቶች ከእሬቻ በአል ላይ ተሰሙ ተቃውሞው በከፍተኛ አይሎአል ፣ ህዝብ መንግስትን አልተቀበለውም ! መንግስት ግን በግዳጅ እመራለሁ ብሎ ሙጥኝ ብሎአል
Read More →የትነበረሽ ንጉሴ ማን ናት? ስለሥራዋ፣ ስለ አስተዳደጓ፣ የዓይኗን ብርሃን እንዴት እንዳጣች፣ ስለ ልጆቿ ….. እንዲህ ትላለች።
(ምንጭ ድንቅ መጽሔት አትላንታ) ከሦስት ዓመት በፊት የድንቅ መጽሔት የአዲስ አበባ ሪፖርተር ጽጌ ዓይናለም የትነበርሽ ንጉሴን እና የሚያውቋትን አነጋግራ የሚከተለውን አጠናቅራ ነበር። የሰሞኑ የየትነበርሽን ስኬት ምክንያት አድርገን እንደገና አቀረብነው። አሜሪካ የሚገኘው Center for the Right of Ethiopian Women የተባለ ድርጅት “የዘመኑ ጣይቱዎች”ብሎ በአሜሪካና በኢትዮጵያ የሚገኙ አስር ተፅዕኖ ፈጣሪ ሴቶችን መርጧል፡፡ ከእነዚህ ሴቶች መካከል የትነበርሽ ንጉሴ […]
Read More →የአካል ጉዳተኞች ተከራካሪዎች የትነበርሽ ንጉዜ ትክክለኛ ህይወት ሽልማት ተቀበለች በአራት ዓለም አቀፍ ተሟጋቾች ለ ‘የአማራጭ የኖቤል ሽልማት’ ተሰጥቷል
የአካል ጉዳተኞች ተከራካሪዎች የትነበርሽ ንጉዜ ትክክለኛ ህይወት ሽልማት ተቀበለች በአራት ዓለም አቀፍ ተሟጋቾች ለ ‘የአማራጭ የኖቤል ሽልማት’ ተሰጥቷል የኢትዮጵያ ጠበቃ የትምህርት ዕድልን እና በአፍሪካ እና በአለም ዙሪያ የአካል ጉዳት ማህበረሰቡን ለመደገፍ ሽልማቱ ለዓለም አቀፍ ችግሮች ተግባራዊ መፍትሄ ያገኘችውን እድል አክብራለች.የሕይወት ሽልማት አሸናፊ 5 ዓመት ሲሞላው አይንዋ ማየት አልቻለም ሆኖም በቤተሰብዎ ውስጥ ያሉ አንዳንድ ሰዎች እርግማን […]
Read More →አሳዛኝ መረጃ … የአለማችን ወፍራሟ ሴት አረፈች :(
================================= * ግብጻዊዋ ኢማን 500 ኪሎ ትመዝን ነበር * ያረፈችው አቡዳቢ ውስጥ ቡርጅ ሆስፒታል ነው 500 ኪሎ ግራም በመመዘን በአለማችን ወፍራሟ ሴት እንደሆነች የምትገመተው ግብጻዊዋ እመቤት ኢማን አብ ኢል አታይ ዛሬ ሰኞ መስከረም 15 ቀን 2010 ዓም ማረፏ ከዱባይ የተሰራጨው መረጃ ያስረዳል ። ከአሌክሳንደርያ ግብጽ ወደ ህንድ በመጓዝ የተሳካ ህክምና ካደረገች በኋላ ከወራት በፊት ወደ […]
Read More →ቴዲ አፍሮ “ሎሬት” በሚለው የክብር ማዕረግ የመጠራት ፍላጎት እንደሌለው ተገለጸ
እጅግ በጣም ተወዳጁ ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ! በኪነጥበብ ሙያ ላበረከተው የጎላ አሰተዋአዖኦ የተለያዩ ሽልማቶች የተበረከተለት ሲሆን ወደፊትም በአገር ውስጥ እና በውጪ የሚበረከትለት ሽልማት እንዳለ መረጃዎች ያመላክታሉ። ድምጻዊ ቴዲ አፍሮ በአገር ውስጥ እና በውጪ የተበረከተለት ሽልማት እንደተጠበቀ ሆኖ፤ በአቢሲንያ የሽልማት ድርጅት አማካኝነት ቴዲ አፍሮ በኪነጥበብ ዘርፍ ሁለንተናዊ አስተዋጽዖ የ”ሎሬት” የክብር ማዕረግ መጠሪያ ስም መስጠቱ […]
Read More →‘አጃኢብ’ ያሰኘው የአዜብ መስፍን ወሬ ክንፉ አሰፋ
“አከ’ሲ” አለ ያገሬ ሰው፣ ከሰሞኑ ‘አጃኢብ’ ያሰኘውን የአዜብ መስፍን ወሬ ሲሰማ። አዜብ ልምድ ያላት ውሸታም እንጂ ልምድ ያላት ኮሜዲ አትመስልም ነበር። ከሚሚ ስብሃቱ ጋር በያዝነው ሳምንት የተወኑትድራማ ግን ጦሽ አርጎ ያስቃል። መቼም ጥርስ እንጂ ልብ አይስቅ። ፈንድሻም’ኮ ልቧ እየተቃጠለ ነው ፊትዋ ሚፈካው። ሴትየዋ አይኗን ሳይሆን ቅንድቧን በጨው አጥባ “ምንም የለኝም ግን ይወረስ” ነው የምትለው። መለስ የባንክ ደብተር ይቅርና መንጃ ፈቃድ እንኳ የለውም ስትል የቀለደችበት ወቅት ሩቅ አይደለም። እርግጥ ነውአዜብ በራስዋ ስም እንኳን ሕንጻ፣ ሲም ካርድም ሊኖራት አይችልም። ጥሩ ጋዜጠኛ አልገጠማትም እንጂ፣ ቢገጥማት፣ “እመኑኝ ልጃገረድ ነኝ!” ብላ እያለቀሰችም ቢሆን ለማሳመን ትሞክር ነበር። ልጆቼን እየተበደርኩ ነው የማስተምረው ብላ በተናገረች ሰሞን ኤ.ቢ.ሲ ኢንተርናሽናል የተባለው የማድሪድ ጋዜጣ ወ/ሮ አዜብ መስፍን በአንድ ቀን የግል ግብይት ብቻ 1.5 ሚሊዮን ዶላር እንዳወጣች ዘግቦ ነበር። የወዲ ስብሃቱ ልጅ አላማ ‘የሙስናዋን ንግስት’ ነጻ ለማውጣት መሞከር ባይሆን ኖሮ ፣ በነካ እጅዋ ሰሞኑን በወደቀ ሂሳብ እየተቸበቸቡ ስላሉ የአዲስ አበባ ሕንጻዎች ጉዳይ ታነሳ ነበር። የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ጠቅልሎ የያዘው ኤፈርት አናት ላይ ቁጭ ብላ “ምንም የለኝም” የሚል ነጠላ ቀልድ የለቀቀችው አዜብ 30 ሚሊዮን ብር ከኪስዋ መዝዛ ለመቀሌ ስፖርት ክለብ መለገስዋን እንኳ ረስታዋለች።ግብር የማይከፍልና የኦዲት ቁጥጥር የማይነካው ደጀና የተባለው የማፍያ ኩባንያ ከኤፈርት ጋር ተጣምሮ የሃገሪቱን ኢኮኖሚ እኩሌታ ይዟል። ካፒታሉ አፍሪካ አንደኛ የሆነው የዚህ ጥምር CEO ነኝ ብላናለች አዜብ። ሰማይአይታረስ፣ ንጉስ አይከሰስ፣ ደሞዝ አይነገር.. ደሞዝ አይጠየቅ! በዛሚ! “ዛሚ ኤፍ.ኤም “ ተብሎ በሚጠራው የነሚሚ ስብሀቱ ራዲዮ ጣቢያ ከዚህ ቀደም የሞራል ቀውስ ውስጥ ገብተው የሚዋኙ ትናንሾችን እያቀረበ፣ በደረቀ ፕሮፓጋንዳ ብቻ ብዙ መጓዝ ባለመቻሉ፣ የፕሮግራም ለውጥያደረገ ይመስላል። እንደ አዜብ መስፍን አይነቱን ጥያቄና መልስ እያስጠና ተከታታይ ድራማ ማቅረብ ጀምረዋል። የመጀመርያው ሾው በቴዲ አፍሮ ተጀመረ ። ገድለው ሃውልት መስራት ለነሱ አዲስ ነገር አይደለምና ጸሃይየሞቀውን “እርምጃው ፍትሃዊ አይደለም” እንቶፈንቶ ደጋገመችው። የቴዲ አፍሮን የአልበም ምረቃ ያገደውን ስውር እጅ አደባብሳ አለፈችው። ስለማታውቀው ፍትህ እና መብት መለፈፍዋ ግን ብዙዎችን ሳያስደምምአልቀረም። አዜብ በተከታዩ ክፍል ብቅ ብላ፣ “የምተዳደረው በደመውዝ ነው። መለስም፣ እኔም፣ ልጆቼም ሃፍት የላቸውም።” አለችን። “ውልና ማስረጃ የሌለው ሃፍት ካለኝ ቦታውን ያሳዩኝ እና ለኢትዮጵያ ህዝብ ልመልሰው” የሚለው ሕጻን ልጅን እንኳ የማያሳምን አባባልዋ ትንሽ ያስቃል። ሕዝብ በደቦ ወጥቶ የአዜብና ዘመዶችዋን የልተመዘገበንብረት እንዲያፈላልግላት መጠየቅዋ ነው ወይንስ የእሷም ህንጻዎች እንደ ኮንዶሚኒየሙ “ጠፍተዋል” ብለው ነገሯት? ከሠበታ የወሰደችው 1200 ሄክታር መሬት የቀብርዋ ስፍራ መሆኑ ነው። ይህ ደግሞ በነሱ ቋንቋ ሙስና አይባልም። ሙስናም ቢሆን ለከባባድ ሚዛን የህወሃት አባላት የአገልግሎት ስጦታ ነው። አቶ አያሌው መንገሻ፣ የቀድሞው የደህነት መ/ቤት ሹም ህብር ሬዲዮ ራይ ቀርበው በሰጡት ቃለ ምልልስ “በሕወሃት ሙስና ወንጀልአይደለም” ብለውናል። ኮሜዲያን ወደ ውጭ ሲሰደዱ፣ ፖለቲከኞቹ ቦታቸውን ይዘዋል ልበል? ከሰሞኑ የህወሃት ካድሬዎች እንደጉድ መቀለድ ጀምረዋል። አዜብ እና ከሚሚ ተደራጅተው […]
Read More →
