www.maledatimes.com ቅ/ሲኖዶስ ስለ ዐራተኛው ፓትርያሪክ፣ ዕርቀ ሰላምና ስለ ስድስተኛው ፓትርያሪክ ምርጫ ያሳለፋቸው ውሳኔዎች - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

ቅ/ሲኖዶስ ስለ ዐራተኛው ፓትርያሪክ፣ ዕርቀ ሰላምና ስለ ስድስተኛው ፓትርያሪክ ምርጫ ያሳለፋቸው ውሳኔዎች

By   /   January 16, 2013  /   Comments Off on ቅ/ሲኖዶስ ስለ ዐራተኛው ፓትርያሪክ፣ ዕርቀ ሰላምና ስለ ስድስተኛው ፓትርያሪክ ምርጫ ያሳለፋቸው ውሳኔዎች

    Print       Email
0 0
Read Time:3 Minute, 3 Second
  1. ሥልጣነ ፕትርክና ሲፈልጉ ተረከቡኝ፣ ሲፈልጉ መልሱኝ እየተባለ የሚከራከሩበት ሥልጣን ባለመኾኑ ዐራተኛውን ፓትርያሪክ ወደ መንበረ መመለስ በቤተ ክርስቲያን ቀኖና ውስጥ ሥርዐተ አልበኝነት እንዲሰፍን መፍቀድ ነው፡፡ ከዚህም ጋራ አምስተኛው ፓትርያሪክ በሕገ ቤተ ክርስቲያን ተሹመው የተሠራው የኻያ ዓመታት ሥራ ደምስሶና ሠርዞ ወደኋላ በመመለስ ዐራተኛው ፓትርያሪክ ብሎ መቀበል ፍጹም የማይቻል በመኾኑ፣ የቀድሞው ዐራተኛ ፓትርያሪክ በፓትርያሪክነት የሥልጣን ደረጃ እንደማይቀበል ቅዱስ ሲኖዶስ በማያሻማ ኹኔታ በድጋሚ ወስኖአል፡፡
  2. ቤተ ክርስቲያን በአሁን ጊዜ ከዚህ በላይ ያለመሪ ለብዙ ጊዜ እንድትቆይ ማድረግ መንፈሳዊና ማኅበራዊ ሥራዋ እንዲስተጓጎል፣ መልካም አስተዳደሯም እንዲዳከም የሚያደርግ ስለኾነ ቀደም ሲል በተወሰነው መሠረት የስድስተኛው ፓትርያሪክ ምርጫ ሕገ ቤተ ክርስቲያንነና ቀኖናው ተጠብቆ የምርጫው ሂደት እንዲቀጥል ወስኗል፡፡
  3. ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ምንጊዜም የሰላምና የአንድነት መሪ እንደመኾኗ    መጠን የተጠቀሱት አባቶች የተሰጠውን የሰላም ዕድል ተጠቅመው ወደ ሰላሙና አንድነቱ ለመምጣት ፈቃደኞች ኾነው እስከተገኙ ድረስ ኹኔታዎች ሲመቻቹ ቀደም ሲል የተጀመረውን የሰላምና ዕርቅ ሂደት እስከመጨረሻው ድረስ ለማስቀጠል አሁንም ቤተ ክርስቲያናችን ዝግጁ መኾኗን ቅዱስ ሲኖዶስ በማረጋገጥ ጉባኤውን አጠናቋል፡፡

የመግለጫውን ሙሉ ቃል ከዚህ በታች ይመልከቱSynod Decision 001Synod Decision 002Synod Decision 003Synod Decision 004Synod Decision 005

 
Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 11 years ago on January 16, 2013
  • By:
  • Last Modified: January 16, 2013 @ 2:11 pm
  • Filed Under: Ethiopia
  • Tagged With:

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar