www.maledatimes.com የ“ኢትዮ ምህዳር” ዋና አዘጋጅ እንደገና ተከሰሰ - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

የ“ኢትዮ ምህዳር” ዋና አዘጋጅ እንደገና ተከሰሰ

By   /   December 31, 2013  /   Comments Off on የ“ኢትዮ ምህዳር” ዋና አዘጋጅ እንደገና ተከሰሰ

    Print       Email
0 0
Read Time:3 Minute, 9 Second

የኢትዮ ምህዳር ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ጌታቸው ወርቁ፤ ከንግድ አሰራርና ሸማቾች ባለስልጣን ጋር በተገናኘ ሐሙስ እለት ማዕከላዊ ምርመራ ድረስ ተጠርቶ ቃል እንዲሰጥ ተደረገ፡፡ በባለስልጣኑ ለፖሊስ ያመለከተው፣ ህዳር 23 ቀን 2006 ዓ.ም “የንግድ አሰራርና ሸማቾች ባለስልጣን ቅሬታ ቀረበበት” በሚል ርእስ በጋዜጣው ላይ ባወጣው ዜና ሳቢያ እንደሆነ ጋዜጠኛ ጌታቸው ተናግሯል፡፡ የመስሪያ ቤቱ ሰራተኞች ቢሯችን ድረስ መጥተው የዜና ጥቆማ ሲሰጡን፤ መስሪያ ቤቱ ዘመድ አዝማድ በሙስና የሚሰባሰቡበት ሆኗል በማለት የጽሑፍና የቃል መረጃ አቅርበውልናል የሚለው ጋዜጠኛ ጌታቸው፤ ጋዜጠኛ ልከን ስራ አስኪያጁን ለማነጋገር ብንሞክርም ሳይሳካ ወደ ህዝብ ግንኙነት ክፍል እንድንሄድ ነው የነገረን ብሏል፡፡ እዚያም ቢሆን ጥያቄዎቻችሁ ኢሜይል አድርጉልኝና መልስ እሰጣለሁ ብሎ እንደዘገየብንና እንዳልተሳካልን አካተን ዜናውን ሰርተነዋል ብሏል ጋዜጠኛው፡፡ በ15 ቀኑ በኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን በኩል ቅሬታ ሲደርሰን፤ ቅሬታ ካለው እናስተናግዳለን ብለን መልስ ሰጥተናል ያለው ጋዜጠኛ ጌታቸው፤ ሐሙስ እለት ወደ ማእከላዊ ምርመራ ተጠርቼ ቃሌን እንድሰጥ ከተደረግሁ በኋላ በዋስትና ተለቅቄያለሁ ብሏል፡፡ “ኢትዮ ምህዳር” ጋዜጠኞች በአዋሳ ዩኒቨርሲቲ ክስ ቀርቦባቸው በቀጠሮ ቀን ለመከራከር በተጓዙበት አጋጣሚ በስራ ባልደረባቸው ላይ አደጋ እንደደረሰባቸው ይታወሳል፡፡ ለሁለት ቀናት በለገጣፎ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው እንደነበረም አዘጋጁ ተናግሯል፡፡

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 10 years ago on December 31, 2013
  • By:
  • Last Modified: December 31, 2013 @ 9:45 am
  • Filed Under: Ethiopia
  • Tagged With:

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar