www.maledatimes.com ዶክተር ዳኛቸው አሰፋን ከዩኒቨርስቲ ለማባረር የተሰራው ሴራ ከሸፈ:: - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

ዶክተር ዳኛቸው አሰፋን ከዩኒቨርስቲ ለማባረር የተሰራው ሴራ ከሸፈ::

By   /   April 1, 2014  /   Comments Off on ዶክተር ዳኛቸው አሰፋን ከዩኒቨርስቲ ለማባረር የተሰራው ሴራ ከሸፈ::

    Print       Email
0 0
Read Time:3 Minute, 13 Second

ኑሯቸውን ከመሰረቱባት አሜሪካ ጓዛቸውን ጠቅልለው አገራቸው በ1997 ግድም የገቡት ዶክተር ዳኛቸው አሰፋ ላለፉት ሰባት አመታት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፍልስፍና መምህር በመሆን ሲያገለግሉ ቆይተዋል፡፡

ዶክተሩ በአደባባይ ሀሳባቸውን መግለጽ በመጀመራቸውና ተማሪዎቻቸውም በሀሳብ ላይ ተመስርተው ሀሳባቸውን እንዲገልጹ ማደፋፈር መጀመራቸው በገዢው ፓርቲ ሰዎች በስጋት እንዲታዩ አድርጓቸዋል፡፡
ዳኛቸው የቀድሞዋ የትምህርት ሚኒስትር ገነት ዘውዴ የቅርብ ዘመድ በመሆናቸውም‹‹የራሳችን ሰው እንዴት በአደባባይ ይተቸናል››የሚል ክፉ መንፈስ የተጠናወታቸው ለኢህአዴግ ቅርበት አለን የሚሉ ካድሬዎች ዶክተሩን ከዩኒቨርስቲው ለማስወጣት የተለያዩ ሴራዎችን በመጎንጎን ላይ ታች ሲሉ ቆይተዋል፡፡

የፍልስፍና ምሁሩ የአመት እረፍታቸውን አጠናቅቀው በቅርቡ ወደ ስራ ገበታቸው እንደተመለሱ ዩኒቨርስቲው የቅጥር ኮንትራታቸውን ለማደስ መዝገብ ቤት የሚገኘውን መረጃቸውን ፈልጎ በማጣቱ ኮንትራታቸውን ለማደስ መቸገሩን ያረዳቸዋል፡፡

አስተማሪነትን ለእንጀራ የማይፈልጉት ዳኛቸው በሰሙት ነገር ሳይደናገጡ በየመዝገብ ቤቱ መረጃቸውን ማፈላለጉን ይያያዙታል፡፡አራት መዝገብ ቤት የጠፋው ፋይል ዛሬ ከመዝገብ ቤት ውጪ በአንድ ሰው አማካኝነት በመገኘቱም የመምህሩ የቅጥር ኮንትራት እንዲታደስ ትዕዛዝ ተላልፏል፡፡
ለዳኛቸው ቅርበት ያላቸው ምንጮቼ እንደነገሩኝ ከሆነ‹‹ዛሬ የድል ቀኔ ነው››በማለት ዶክተሩ ለወዳጆቻቸው ተናግረዋል፡፡

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 10 years ago on April 1, 2014
  • By:
  • Last Modified: April 1, 2014 @ 12:28 pm
  • Filed Under: Ethiopia
  • Tagged With:

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar