www.maledatimes.com ዜና በጨዋታ፤ ኢህአዴግ መለስን ሳይተካ ስብሰባውን ቋጨ - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

ዜና በጨዋታ፤ ኢህአዴግ መለስን ሳይተካ ስብሰባውን ቋጨ

By   /   September 5, 2012  /   Comments Off on ዜና በጨዋታ፤ ኢህአዴግ መለስን ሳይተካ ስብሰባውን ቋጨ

    Print       Email
0 0
Read Time:3 Minute, 33 Second

የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ትላንት እና ከትላንት በስተያ በስብሰባ ተወጥሮ ነበር የዋለውና ያመሸው።

በርካቶች ከስብሰባው በኋላ ቀጣዩን የኢህአዴግ ሊቀመንበር ለማወቅ በጉጉት ሲጠብቁ ቢቆዩም ስራ አስፈፃሚው ግን ሊቀመንበሩን ሳይተካ ስብሰባውን ጨርሷል። ኢህአዴግ በድረ ገፁ ላይ የመሪውን ሹመት አስመልክቶ፤ “የተጓደለው አመራር በሚሰየምበት አቅጣጫ ዙሪያ…  የአመራር ምደባ ጉዳይ ለጋራ ዓላማ በሚደረግ ትግል ውስጥ አንድን ጓድ ይበልጥ መስዋዕት ይከፍል ዘንድ ከመመደብ ያለፈ ትርጉም የሌለው ቀላል ጉዳይ…” ሲል የገለፀው ሲሆን፤ በመስከረም የመጀመሪያው ሳምንት የኢህአዴግ ምክር ቤት በሚያደርገው ስብሰባ ላይ ሊቀመንበሩን እንደሚያሳውቅ አትቷል።

በነገራችን ላይ 1
በአቶ መለስ መሞት ሳቢያ፤ የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር፣ የጦር ሃይሎች አዛዥ፣ የኢህአዴግ ሊቀመንበር፣ የህውሃት ሊቀመንበር እና ሌሎችም እኔ ደክሞኝ ወይም ረስቼ የተውኳቸው ቦታዎች ክፍት ሆነው እየጠበቁ ነው።

በነገራችን ላይ 2
በጋና ፕረዘዳንቱ አቶ ሚልስ የሞቱ ጊዜ ምክትላቸው ቃለ ማህላ ፈፅመው ቦታቸውን የተኩት ከቀብር በፊት ነበር። ምክንያቱን ስንጠረጥር በጋና ከቀብር ይልቅ ሀገር ይበልጣል! በኢትዮጵያስ…!? ተብሎ አይጠየቅም…!

በመጨረሻም፤
በአንድ ወቅት የኤርትራው ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር የነበሩት አሊ አብዶ ሞቱ። አቶ ሲሳያስ እና ጓደኞቻቸውም ለእኒህ ሰው ትልቅ አክብሮት ነበራቸው አሉ። ለክብራቸው መገለጫም ሲሉ ለሁለት አመታት ያኽል ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ሳይሾሙ ቀሩ። አሁንም በነገራችን ላይ ለኤርትራ ቅርበት እንዳላቸው የሚነገርላቸው አቶ በረከት ስምዖን ምነውሳ ጠፉ…!? እስቲ በቅርብ የምታገኘቸው ጠይቁልኝ ይሄንን የኤርትራ ልምድ ለኛም ሀገር ይጠቀሙት ይሆንን!

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 12 years ago on September 5, 2012
  • By:
  • Last Modified: September 5, 2012 @ 11:38 pm
  • Filed Under: Ethiopia
  • Tagged With:

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar