www.maledatimes.com ጃንጥላው ተቀዶአል - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

ጃንጥላው ተቀዶአል

By   /   September 10, 2012  /   Comments Off on ጃንጥላው ተቀዶአል

    Print       Email
0 0
Read Time:5 Minute, 14 Second

           የወያኔ ስርአት በታሪኩ እንዲህ ያለ የተምታታ ሁኔታ ላይ የደረሰበት የታሪክ አጋጣሚ ነበር ለማለት አይቻልም። የባንክ ሰራተኞች የስራ ማቆም አድማ፣ የኦነግ ከመሸጋገሪያው መውጣት፣ የኤርትራ ጦርነት፣ የህወሃት መከፋፈል፣ ምርጫ 97 የመሳሰሉ አጋጣሚዎች ለኢህአዴግ ፈታኝ የነበሩ መሆናቸው ይታወቃል።

ከፍተኛ ትርምስ የነበረባቸውም ናቸው። ቢሆንም በነዚያ ጊዜያት ድርጅቱ ድርጅታዊ አቅሙን ባለማጣቱ አንሰራርቶ መቀጠል ችሎአል። የመለስ ዜናዊን እረፍት ተከትሎ የመጣው ቀውስ ግን የድርጅቱን መሰረት እያናጋው ይገኛል።

        መለስን ተከትሎ አብሮ ለመሞት በጣም እየተጣደፈ ያለው ኦህዴድ ሆኖአል። ኦህዴድ መሪ የለውም። የህወሃት አንጋፋዎች የራሳቸው ችግር ቢኖርባቸውም ኦህዴድን ከመሞት ለማዳን ቅድሚያ ትኩረት ሰጥተው እየተሯሯጡ ይገኛሉ። መተካካት የሚለውን ነጠላ ዜማ ደምስሰው፣ ገራባ እየፈለጉ ነው። መገረብ ጀምረዋል። ኩማ ደመቅሳን የኦህዴድ ሊቀመንበር፣ አባ ዱላን በኦሮሚያ ፕሬዚዳንትነት ለማስቀመጥ፣ በካድሬዎቻቸው በኩል ቅስቀሳ ይዘዋል። ይህ ሩጫ ጊዚያዊ ጥገና ይባላል። እንደ አሸዋ ግድብ ከነገ ወዲያ መልሶ ይፈርሳል።
“የሃይለማርያም ደሳለኝ ምክትል ማን ይሁን?” የሚለው እንዳከራከረ ሲሆን፣ በአንድ በኩል ሶስት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮችን ለማስቀመጥ አሳብ ሲቀርብ፣ በሌላ በኩል የህወሃት እና የብአዴንን ፉክክር ለማስቀረት፣ ኩማ ደመቅሳን በምክትልነት ለማስቀመጥ መምረጣቸው ይሰማል። መፍትሄ አይሆንም። በዚህ አካሄድ ማንኛውም ነገር ወደሁዋላ በፍጥነት ይጓዛል።
ሁኔታዎች በፍጥነት ሲለዋወጡ ሰንብተዋል። ለዚህ ሲለዋወጥ ለሰነበተ ውዥንብር መቁዋጠሪያ ለማበጀት የኢህአዴግ ምክርቤት ከመስከረም 3 እስከ 5 ስብሰባ ጠርቶአል። ርግጥ ነው፣ ውዥንብሩን ለመቀነስ የሚረዳ፣ ከሃሜት የሚያድናቸውን አንድ ደካማ መዋቅር በመፍጠር፣ “ችግሩ ተፈትቶአል” ብለው ሊውጁ ይችላሉ።
ሊቀጥሉ ግን አይችሉም። ኢህአዴግ ማእከል አጥቶአል። ቀደም ሲል ኢህአዴግ አንድ መቋጠሪያ ነበረው። አንድ የሚፈሩት ሰው ነበራቸው። ሁሉም ልዩነቱን፣ ቅሬታውን ብሶቱን ይዞ የሚሮጥበት አንድ ቢሮ ነበር። አሁን ያ የለም። ጃንጥላው ተቀዶአል። ከጥቂት በላይ ምሰሶዎች በያቅጣጫው እየተተከሉ ነው። በራቸውን መክፈት ካልቻሉ፣ አፍጦ የመጣባቸውን እውነት ማየት ካልቻሉ እጣ ፈንታቸው ደጃፋቸው ላይ ከተቀመጠው መልአከ ውድቀት እጅ ላይ መውደቅ ይሆናል።
Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 12 years ago on September 10, 2012
  • By:
  • Last Modified: September 10, 2012 @ 6:01 pm
  • Filed Under: Ethiopia
  • Tagged With:

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar