www.maledatimes.com በነ እስክንድር ላይ አስገራሚ ውሳኔ ተላለፈ።በውርስ ያገኘው ቤት እንዲነጠቅ ተብሏል ዘገባው የደረጀ ሃብተወልድ ነው ! - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

በነ እስክንድር ላይ አስገራሚ ውሳኔ ተላለፈ።በውርስ ያገኘው ቤት እንዲነጠቅ ተብሏል ዘገባው የደረጀ ሃብተወልድ ነው !

By   /   September 20, 2012  /   1 Comment

    Print       Email
0 0
Read Time:5 Minute, 18 Second

በነ እስክንድር ላይ አስገራሚ ውሳኔ ተላለፈ።
1-እስክንድር ነጋ ፦በስሙ ተመዘገበ ባለ አንድ ፎቅ ቤት እና <<በውርስ ከቤተሰቡ ያገኘው ‘ግራውንድ ፕላስ ቱ’ ቤት
2-አንዷለም አራጌ በስሙ የተመዘገበ አንድ መኪና እና
3-አበበ በለው በሚስቱ ስም የተመዘገበ <<ግራውንድ ፕላስ ዋን>> ቤት እንዲታገድ ተብሎ ነው ውሳኔ የተላለፈው።
ስለማውቀው ልናገር፦

በጣም የሚገርመው ነገር፤ እስክንድር ነጋ እናቱ ከማረፋቸው በፊት ቤታቸውን ሲያወርሱት፦” አልፈልግም !”በማለት ውርሱን ያልተቀበለ ሲሆን፤ አሁን እንዲታገድ የተባለው በውርስ የተገኘ ቤት የእርሱ ንብረት አለመሆኑ ነው።
በአጭሩ ላብራራ፦ውርሱ የሚገባው ለእሱ በመሆኑ ብቻ ሳይሆን፤ እናቱ በጣም የሚወዱትና የሚሣሱለት ብቸኛ ልጃቸው ስለሆነ ጭምር ሽማግሌዎችን ሰብስበው የቤቱን ኑዛዜ እንዲቀበል ይጠይቁታል። እስክንድር ግን ገንዘብና ንብረትን አስቀድሞ የናቀ ልጅ በመሆኑ ፤ ከአቋሙ ሊነቃነቅ አልቻለም። በመጨረሻም ቤቱ የአባቱ ልጅ ለሆነች እህቱ ተሰጠ። ውርሱ ለእሷ ጸና።
ዛሬ ይህ የእህቱ ቤት ነው እንዲታገድ የተወሰነው። የእስክንድር እህት፤እህት በመሆኗ ብቻ ንብረቷ ታገደባት። ከእስክንድር ቤተሰብ መወለዷ፤ እንደ ወንጀል ተቆጠረባት።ቤቷን አጣች።
ቢሆንም፤የፍትህ መዛባት ጉዳይ ያሳዝነው ካልሆነ በስተቀር ይህ የቤት ማገድ ውሳኔ ከንብረት ማጣት ጋር በተያያዘ እስክንድርን ቅንጣት ታህል እንደማይጎረብጠው እርግጠኛ ነኝ። እንደውም በውሳኔው ላይ አስተያዬት እንዲሰጥ ቢጠየቅ ኖሮ በደስታ ፦” ሌላ የምትፈልጉትና የቀረ ነገር ካለ ጨምራችሁ ውሰዱ”ሊላቸው እንደሚችልም እገምታለሁ።ለእስክንድር፦ መቀበል ዕዳ፤መስጠት ብጽዕና መሆኑን አውቃለሁና።አዎ <ከሚቀበል የሚሰጥ ሰው ብጽዕ ነው>እንዲል መጽሐፉ፤ እስክንድር መስጠት እንጂ መቀበል አይወድም።ደሞ ለቤት ንብረት!
እንዴ! ከሁለት ዓመት እስር ቆይታ በሁዋላ፣ ከሁለት ዓመት ሥራ መፍታት በሁዋላ፣ የቢሮ ንብረቶቻቸው ተወርሰውባቸው ፣በሥራ እንዳይሰማሩ ተከልክለው ..እና በሌሎች ብዙ ተግዳሮቶች ውስጥ ሆነው በነበረበት በዚያ ወቅት እንኳ ሰርካለም የተሸለመችውን 5 ሺህ ዶላር፤ በችግር ላሉ ጋዜጠኞች መርጃ ይውል ዘንድ ለዓለማቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተንከባካቢ ኮሚቴ(ሲፒጄ) ያበረከቱኮ ናቸው-ጀግኖቹ ጥንዶች።
አንድ ነገር ግን ሁላችንንም አሳዝኖናል-ከኢዲሱ አመራር ጋር በብልጭታ መጠንም ቢሆን ብቅ ትል ይሆናል ብለን በተስፋ የጠበቅናት የፍትሕ ፀሀይ ይብስ እያዘቀዘቀች መሄዷ።
አቶ ሀይለማርያም፤ ይህን እያዩና እየሰሙ ነው? ?
Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 12 years ago on September 20, 2012
  • By:
  • Last Modified: September 20, 2012 @ 12:33 am
  • Filed Under: Ethiopia
  • Tagged With: ,

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%

One thought on “በነ እስክንድር ላይ አስገራሚ ውሳኔ ተላለፈ።በውርስ ያገኘው ቤት እንዲነጠቅ ተብሏል ዘገባው የደረጀ ሃብተወልድ ነው !

  1. Oh God what’s going on? when we hope finally they will take a different course of action that what they did in the past. Is Ethiopia becoming anarchy state.

    I understand PM Hailemaria is just a symbol. I know he been exposed to western life style he knows well, how dear and important it’s to have Freedom Of Speech & Free Press, he really need to do a bit more than praying. God brought you to decision making if you don’t agree in their ruling you can protest by steping down.

    The worl then can see and take action to support the opposition. Why is it necessary to confiscate Mr. Eskinders property or his family when it’s time to release him and direct the country to a new day.

    We are losing hope and believe that any progress will come out of this regime.

Comments are closed.

<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar