www.maledatimes.com ‹‹መሬት ለሱዳን ይሰጥ ብዬ አልፈርምም፣ እናንተ ብትስማሙም እኔ አላስፈጽምም›› አቶ አያሌው ጎበዜ - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

‹‹መሬት ለሱዳን ይሰጥ ብዬ አልፈርምም፣ እናንተ ብትስማሙም እኔ አላስፈጽምም›› አቶ አያሌው ጎበዜ

By   /   September 25, 2012  /   2 Comments

    Print       Email
0 0
Read Time:6 Minute, 42 Second

‹‹መሬት ለሱዳን ይሰጥ ብዬ አልፈርምም፣ እናንተ ብትስማሙም እኔ አላስፈጽምም›› አቶ አያሌው ጎበዜ

 በ1999 ዓ.ም በኢትዮጵያ እና በሱዳን መካከል ተነስቶ የነበረውን የድንበር ይገባኛል ጥያቄ ተከትሎ የተወሰኑ መሬቶችን ከጎንደር ላይ በመውሰድ ለሱዳን ለመስጠት በተደረገው ስምምነት ላይ ፊረማቸውን እንዲያኖሩ የተጠየቁት አቶ አያሌው ጎበዜ በእምቢተኝነት ሲፀኑ በወቅቱ ምክትላቸው የነበሩት የአሁኑ አዲሱ ተሿሚ ም/ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ደመቀ መኮንን ፊርማቸውን ማኖራቸው ይታወሳል፡፡
አቶ አያሌው ጎበዜ በወቅቱ ‹‹መሬት ለሱዳን ይሰጥ ብዬ አልፈርምም፣ እናንተ ብትስማሙም እኔ አላስፈጽምም›› በማለታቸው አቶ በረከትን ጨምሮ የብአዴን አመራሮች ተበሳጭተውባቸው ነበር።
አቶ አያሌው ጎበዜ በችሎታና በልምድ ከአቶ ደመቀ መኮንን የተሻሉ ቢሆኑም፣ አቶ በረከት አቶ አያሌው ” በሱዳን ድንበር ላይ ባሳዩት አቋም” ቂም በመያዝ በእርሳቸው ስር ሆነው ሲሰሩ የነበሩትን አቶ ደመቀን ወደ ፊት በማምጣት አቶ አያሌውን እንደተበቀሉዋቸው ታውቋል። አቶ አያሌው አቶ በረከት እንደፈለጉ የሚያሽከረክሩዋቸው ሰው አለመሆናቸው ለከፍተኛው ስልጣን እንዳይታጩ እንዳደረጋቸው የውስጥ ምንጮች ገልጠዋል።
አቶ መለስ ” ምንም ይሁን ምን አቋም ያለው ሰው ይሻላል” በማለት አቶ አያሌው ጎበዜ በስልጣን እንዲቆዩ የተከራከሩላቸው፣ በእነ አቶ በረከት በኩል የሚታየውን የመሰባሰብ እንቅስቃሴ ለመከፋፈል እንዲመቻቸው እንደነበር ታውቋል።
አቶ መለስ የአማራ ክልልን ለሁለተኛ ጊዜ በፕሬዝዳንትነት በመምራት ላይ የሚገኙትን አቶ አያሌው ጎበዜን ከስልጣን እንዳይወርዱ ታድገዋቸው እንደነበር ውስጥ አዋቂ ምንጮቻችን ገለጸዋል፡፡

 አቶ መለስ ‹‹እዚህ ተቋም ላይ ከሰበሰብካቸው ሰዎች ይልቅ ያ የግል ጋዜጣ የሚያዘጋጀው ልጅ የበለጠ ኮሚትመንት አለው፣ እሱ የሚሰራውን ያውቃል፣ ያንተ ሰራተኞች የሚሰሩትን አያውቁም›› በማለት አቶ በረከትን ወርፈዋቸው ነበር ።

 የኢህአዴግ ምንጮች እንደገለጡት ኢህአዴግ በፕሮፖጋንዳው መስክ ለደረሰበት ኪሳራ አቶ መለስ አቶ በረከትን ተጠያቂ አድርገው ነበር።
በአንድ የግንባሩ ስብሰባ ላይ በመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ሠራተኞች ብቃት ማነስ የተበሳጩት አቶ መለስ ‹‹እዚህ ተቋም ላይ ከሰበሰብካቸው ሰዎች ይልቅ ያ የግል ጋዜጣ የሚያዘጋጀው ልጅ የበለጠ

ኮሚትመንት አለው፣ እሱ የሚሰራውን ያውቃል፣ ያንተ ሰራተኞች የሚሰሩትን አያውቁም›› በማለት አቶ በረከትን ወርፈዋቸው ነበር ።
አቶ መለስ ስም ሳይገልጹ በደፈናው ‹‹አንድ ጋዜጠኛ›› ሲሉ ማነፃጸሪያ ያደረጉት የፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅን ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ነው በማለት ምንጮቻችን ገልጸዋል፡፡
በኢህአዴግ ባለሥልጣኖች ዘንድ አቶ መለስ ዜናዊ በግምገማ እና ስብሰባ ወቅት የኮሙኒኬሽን መሥሪያ ቤትን አይተቹም እየተባሉ ይታሙ የነበረ ሲሆን ከላይ የተገለጸውን ትችት ያቀረቡትም ለመጀመሪያ ጊዜ እንደነበር ምንጮቻችን አስረግጠው ገልጸዋል፡፡
አቶ መለስ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤትን በሚንስትር ማዕረግ የሚመሩትን አቶ በረከት ስምዖንን ከሌሎች ሚንስትሮቻቸው እና የፓርቲያቸው አመራሮች የበለጠ እንደሚያቀርቧቸው ይታወቃል፡፡  
Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 12 years ago on September 25, 2012
  • By:
  • Last Modified: September 25, 2012 @ 10:52 am
  • Filed Under: Ethiopia
  • Tagged With:

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%

2 thoughts on “‹‹መሬት ለሱዳን ይሰጥ ብዬ አልፈርምም፣ እናንተ ብትስማሙም እኔ አላስፈጽምም›› አቶ አያሌው ጎበዜ

  1. You mean Ayalew cared so much about Amhara region he refused to sign to give land to the Sudan. Isn’t that ridiculous. In the first place the border issue between Sudan and Ethiopia is handled by the federal government not by region administrators so Ato Ayalew has no say in that. In the second place even if he did have say in the matter these hodams have no consciounce to stand for anything. All they are interested in is eating and drinikng. SO do not make them what they are not. Anyone who can say what you claim to have Ato Ayalew said will not join EPRDF in the first place.

  2. About the issue Land provission ….

    As maintiooned above the issue is too old, what is the important now, for critisism, or to claim the Land?

    What ever the case the two actor were doing in such a way what the Amharic scripts declaier. About the committment, devotion, inefficiency and to all related matter, almost Ato Ayalew and Ato Demeke are the same. They were/are not worried about Amhara and Amhara region. The two leaders were not having good complementarity, rather they were kept each others. Besides, Ato Demeke was/is more submissive than Ato Ayalew. And as that time we all know as Ato Demeke was on the side of Ato Bereket. For your Witness as they did it Ato Demeke gave a chance to went USA. That trip was after the accomplishment of this mission.

    What Ato Ayalew did, of course nothing. Because,that is why he is there still. If he was doing something good with no doubt he would not be there. Aba Dula the Oromia ex presidant is a good example. Not alone in and to Amhara, Meles and his follower did not want such committed and devotion performance. That is why they pick Aba dula from Oromia. So, make clear the issue why you raise now and we are here (Gondar) and can provide you the right information.

    God bless Ethiopia and Ethiopian

Comments are closed.

<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar