www.maledatimes.com የኢትዮጵያዊያኑ ስደተኞች ሰቆቃ ዛሬም ከወደ ደ/አፍሪካ ይጣራል - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

የኢትዮጵያዊያኑ ስደተኞች ሰቆቃ ዛሬም ከወደ ደ/አፍሪካ ይጣራል

By   /   October 15, 2015  /   Comments Off on የኢትዮጵያዊያኑ ስደተኞች ሰቆቃ ዛሬም ከወደ ደ/አፍሪካ ይጣራል

    Print       Email
0 0
Read Time:1 Minute, 49 Second

 

“ይህ አስር ቤት ለእኔ በምድር ላይ ያለ ሴኦል ሆኖ ነው የሚታየኝ” የ 15 አመቱ ኢትዮጵያዊ እስረኛ

በተለያዩ ምክንያቶች ህይወታቸውን ለመለወጥ/ለማሻሻል በማለት ወደ ደቡብ አፍሪካ ለማቅናት ሲሉ በጎረቤት ማላዊ በኩል ለማቋረጥ የሞከሩ በርካታ ኢትዮጵያዊያን ሰደተኞች በፖሊስ ተይዘው የተፈረደባቸወን የገንዘብ እና የእስራት ቅጣት ቢጨርሱም በአሳቃቂው የማላዊ እሰር ቤት ወስጥ ፈዳቸውን እያዩ እንደሚገኙ የፈረንሳዩ የዜና ወኪል (አጃንስ ፈራንስ ፕሬስ ) እሮብ ጥቅምት 14 2015 አኤአ አ ዘግቧል።
“ለተሻለ ኑሮ ወደ ደ/አፍሪካ ለመሻገር የቋመጡት ኢትዮጵዊያን ሰደተኞች ምኞታቸው ቅዠት ሆነ። “ ያለው ዜና ዘገባው ከመዲናይቱ ሎላንግዊ 85 ኪሜ ርቀት ላይ የሚገኘው እና ለ 800 እስረኞች ተብሎ በተገነባው የዲደዛ እስር ቤት ውስጥ ወደ 2,650 የሚጠጉ እስረኞች ከእነዚህ መካከል 317 በላይ ኢትዮጵያዊያኖች ያለ በቂ ምግብ እና ውሃ አቅርቦት እየተሰቃዩ ይገኛሉ ብሏል።የ15 አመቱ ኢያሱ ታዲዮስ ባለፈው ሃምሌ ወር ከ 29 ጓደኞቹ ጋር ማላዊ ውስጥ ታሰረው በፍርድ ቤት የተጣለባቸውን የገንዘብ አና የእሰራት ቅጣት ቢፈጽሙም “ወደ አገራቸው የሚያጓጉዛቸ ተቋም በመታጣቱ ለተጨማሪ ሰቆቃ ተጋልጠዋል ተብሏል።እያሱ ሰለደረሰበት ሰቆቃ ሲናገር “ይህ እሰር ቤት ለእኔ በምድር ላይ ያለ ሲኦል ሆኖ ነው የሚታየኝ። ቀድሞ የነበረኝ ሕልም እና ተሰፋ ሁሉ እዚህ ላይ ተገቷል ። ከ 5 ጓደኞቼ ጋር የተጣለብን 62 ዶላር ቅጣትን ብንከፍልም እና እስራቱን ብንጨርስም እስከ አሁን ድረስ አልተፈታንም ። አሁን የምፈልገው ነገር ቢኖር ወደ አገሬ መመለስ ብቻ ነው ።” በማለት ሰውነቱ በደካም እና በረሃብ የጠወለገው ታዳጊው ወጣት ኢያሱ በማላዊው እስርቤት ውስጥ የደረሰበትን ሰቆቃ እና መጥፎ ገጠመኝ በመግለጽ “የድረሱልን” ጥሪውን አቅርቧል።
ባለፈው መሰከረም ወር በአሜሪካው የሰደተ ተመላሾች ደረጅት አማካኝነት 70 ኢትዮጵያዊያን ሰደተኞች ነፍሳችውን ብቻ አትርፈው ወደ አገራቸው በበጎ ፍቃደተኝነት የተመለሱ ሲሆን በአሁኑ ወቅት በእሰራት ላይ ያሉተን 317 ወገኖቻችንን ወደ ኢትዮጵያ ለማጓጓዝ በትንሹ የ አሜሪካ 200,000 ዶላር እንደሚያሰፈልግ ተገምቷል።የአለም አቀፉ ከሰደት ተመላሾች ድርጀት ተሰፋ የጠፋባቸው ኢትዮጵያዊያኑ ሰደተኞችን ወደ አገራቸው ለማጓጓዝ የበኩሉን ጥረት ቢያደረግም የአለማቀፉ ማህበረሰብ ወቅታዊ ትኩረቱ ወደ መካከለኛው ምስራቅ (የሶሪያ ሰደተኞች) ላይ በመሆኑ አትዮጵያዊያኑ ሰደተኞች አሰተዋሽ አጥተዋል ተብሏል ። የደርጅቱ ዋና ሹም የሆኑት ሚስስ ካትሪን ሳኒ በበኩላቸው “እነዚህ ማስኪን ነፍሳት ከአገራቸው /ከኢትዮጵያ / እርቀው እንደዚህ አይነቱ አሰከፊ ሁኔታ ውስጥ መውደቃቸው በእጅጉ ያሳዝናል” በማለት በኢትዮጵያዊያኑ ሰደተኞች ላይ እየደረሰ ያለው ችግርን በሃዘኔታ ለማስረዳት ሞክረዋል።
በዚህ አጋጣሚ አገሪቱ በኢኮኖሚዋ “አድጋለች፣ ተመንደጋለች፣ ሰላም እና መረጋጋት ዙሪያ ገባዋን ሰፈኖባታል” ከተባለ ለምን ቁጥራቸው ቀላል የማይባል ፖለቲከኞች ያልሆኑ ነገር ግን የወደፊቱ አገር ተረካቢ የሆኑ ሕጻናት እና ወጣቶች አስከፊውን የባህር እና የየብስ ጉዞ በማድረግ ለእንደዚህ አይነቱ እጅግ ዘግናኝ እና አሳቃቂ ችግር ይጋለጣሉ? ብለው የሚጠይቁ ወገኖች ተበራክተዋል።

Tamiru Geda's photo.
Tamiru Geda's photo.
Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 9 years ago on October 15, 2015
  • By:
  • Last Modified: October 15, 2015 @ 10:28 am
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar