www.maledatimes.com ከሰማያዊ ፓርቲ ልዩ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተሰጠ መግለጫ - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

ከሰማያዊ ፓርቲ ልዩ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተሰጠ መግለጫ

By   /   October 13, 2016  /   Comments Off on ከሰማያዊ ፓርቲ ልዩ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተሰጠ መግለጫ

    Print       Email
0 0
Read Time:1 Minute, 49 Second

ሀገራችን ኢትዮጵያ ቀደምት እና ታላቅ ከሚባሉት ሀገሮች አንዷ ብትሆንም፤በሚያጋጥሟት ጨቋኝ ገዢዎች ምክንያት የሀገሮች ሁሉ ጭራ ለመሆን ተቃርባለች፡፡ እስካሁን ድረስ በመረጣቸው መሪዎች ለመተዳደር ያልታደለው የኢትዮጵያ ህዝብ ለምርጫ እና ለዲሚክራሲ ሥርዓት ያለውን ቁርጠኝነት በምርጫ 97 አሳይቷል፡፡ ነገር ግን ትናንትም ሆነ ዛሬ የምርጫ ውጤት መገልበጥ እና ማጭበርበሩን የቀጠለው የህወሐት/ኢህአዴግ አገዛዝ በምርጫ 2007 መቶ በመቶ አሸንፊያለሁ ቢልም በአገዛዙ ላይ ለ6 (ስድስት) ወራት እንኳን ሳይቆይ ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ ተቃውሞ እያስጨነቀው ይገኛል፡፡ የህዝቡም ጥያቄ ግልጽ ነው፡፡ “መሰረታዊ የስርዓት ለውጥ!”
በኦሮሚያ እና በአማራ ክልሎች የተነሳው ህዝባዊ አመጽ እንደሰደድ እሳት እንዲቀጣጠል ያደረገው የ25 ዓመታት ዘረኝነት የግፍ አገዛዝ መሆኑ ለሁላችንም ግልጽ ነው፡፡ በወልቃይት ጠገዴ፣ በኮንሶ፣ በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት፣ በቢሾፍቱ እሬቻ በዓል ላይ እና በሌሎች የሀገራችን ክፍሎች የሚደረገው ግድያ፣ እስራትና ማፈናቀል የአገዛዙ አስከፊነት እና የአገዛዙ ቁንጮዎች ያለ ህዝብ ይሁንታ በስልጣን ለመቀጠል የሚያሳዩት የጭካኔ ደረጃ በግልፅ የሚያመላክት መሆኑ በተለይ ሰማያዊ ፓርቲ በቀደምት መግለጫዎቹ ሲገልጽ ቆይቷል፡፡
ከታሪክም እንደምንረዳው የአምባገነንነት መጨረሻ የውርደት ሞት መሆኑን ነው! ከውድቀት ጥቂት ቀደም ብለው መንቃት የቻሉ አምባገነኖች ሀገራቸውን ከማፍረስ፣ ህዝቡን ከሞት እና ከስደት፣ እራሳቸውንም ከውርደት አድነው ለዲሞክራሲያዊ ስርዓት መሰረት ጥለው ስማቸው በክብር ሲወሳ መኖሩን ነው፡፡ ዛሬ በሀገራችን የምናየው አገዛዝ በመስቀለኛ መንገድ ላይ መቆሙን ነው፡፡ ምርጫውም የሚሆነው ችግሮችን አድበስብሶ ለውድቀት መብቃት ወይም የመሰረታዊ ለውጥ አጋዥ ሆኖ በክብር ስልጣኑን ለህዝብ ማስረከብ ነው፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ “እኔ ከሌለሁ ሀገር ትበታተናለች” የሚለውን የህወሐት/ኢህአዴግ ሟርት አይቀበልም፡፡ ከዚህ ይልቅ የተጀመረው ህዝባዊ አመፅ ተገቢውን ምላሽ ሳያገኝ እንደማይቆም በፅኑ ያምናል፡፡
ስለሆነም ጠቅላላ ጉባዓው የሚከተሉትን ባለሰባት ነጥብ የአቋም መግለጫ አውጥቷል፡፡
1ኛ. ገዢው ፓርቲ ሰላማዊ ተቃውሞ ባነሱ ዜጎች ላይ መተኮሱን እና መግደሉን፣ ማሰርና ማፈናቀሉን በአስቸኳይ እንዲያቆም፡፡ የመከላከያ ሰራዊ ተግባር የሀገርን ዳር-ድንበርና ሉዐላዊንት መጠበቅ መሆኑን ተገንዛቦ በአስቸኳይ ወደ ጦር ካምፑ እንዲመለስ፡፡
2ኛ. እስካሁን የተገደሉና የተጎዱ፣ የተፈናቀሉና የተንገላቱ ወገኖችን ጉዳይ በገለልተኛ አካል እንዲጣራ፡፡ ለዚህ ጥፋት ትእዛዝ የሰጡ ባለሥላጣናትም ለህግ እንዲቀርቡ፡፡
3ኛ. መንግስት የዘጋውን ማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች በአስቸኳይ እንዲከፍት፡፡
4ኛ. የገዢው ፓርቲ ባለስልጣናት እና መገናኛ ብዙሃን ህዝብን ከሚያስቆጡ ተግባራትና ገለፃዎች እንዲታቀቡ፡፡
5ኛ. የተቃዋሚ መሪዎች እና አባላት በቀጣይ የሀገራቸው ሁኔታ ላይ ነፃ ስብሰባ እና ውይይት እንዲያደርጉ፡፡ ይህም መንግስት መሰናክል መፍጠሩን እንዲያቆም፡፡
6ኛ. ገዢው ፓርቲ ከህዝቡ ጋር በመወያየት በአሰቸኳይ ስልጣኑን ለህዝብ የሚያስረክብበትን መንገድ እንዲያመቻች፡፡
7ኛ. ሰማያዊ ፓርቲ በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ያገባኛል ከሚሉ ማናቸውም ኢትዮጵያዊያን ወገኖቹ ጋር ተቀራርቦ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን እየገለፀ፤ ስለሀገራችን ወቅታዊ ጉዳይም አዎንታዊ መፍትሔ የሚያስገኝ ውይይት እንዲጀመር ጥሪውን ያቀርባል፡፡
ኢትዮጵያ በክብር ለዘለአለም ትኑር!
መስከረም 28 ቀን 2009 ዓ.ም

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 8 years ago on October 13, 2016
  • By:
  • Last Modified: October 13, 2016 @ 11:12 pm
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar