www.maledatimes.com የኢድ አልፈጥር እረፍት ፣ የስደተኛው እንግልትና ተስፋ ! - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

የኢድ አልፈጥር እረፍት ፣ የስደተኛው እንግልትና ተስፋ !

By   /   June 21, 2017  /   Comments Off on የኢድ አልፈጥር እረፍት ፣ የስደተኛው እንግልትና ተስፋ !

    Print       Email
0 0
Read Time:1 Minute, 57 Second

የማለዳ ወግ ፣
====================================
* ኢድ አልፈጥር እረፍት በንጉሱ አዋጅ ተራዘመ !
* ተስፈኛው ስደተኛ

ረመዳን ከመግናቱ አስቀድሞ ተማሪዎች ፈተና ወስደው በረመዳን ትምህርት እንዳይኖር በአዋጅ የደነገጉት የሳውዲው ንጉስ ሰልማን ቢን አብድልአዚዝ የዘንድሮው ኢድ አልፈጥር እረፍት ለአንድ ሳምንት እንዲራዘም ትንናት አዋጅ አውጥተዋል ። ንጉስ ሰልማን ቢን አብድልአዚዝ የኢድ አልፈጥር እረፈጥር እረፍት እንዲራዘም በአዋጅ ያዘዙት ትናንት ምሽት መሆኑ ተጠቁሟል ። የሳውዲው ንጉስ ልጃቸውን ልዑል መሀመድን አልጋ ወራሽ ባደረጉበት አዋጅ በመንግስት አስተዳደር በርካታ ሹመትን ለተለያዩ ባልስጣናት ሰጥተዋል ። አዳዲስ አምባሳደሮችም በአዋጅ ሾመዋል ። በቀጣይ ቀናትም ከንጉሱ ተጨማሪ አዋጆች ይጠበቃሉ !

የተስፈኛው ስደተኛ እረፍት …
==================

የሳውዲ ምህረት አዋጅ የፊታችን እሁድ ያበቃል ። የገባው ገብቶ ያልገባው እንዳልገባ ቀርቷል። ለዚህም ፈርጀ ብዙ ምክንታት አለው ፣ 400 ሽህ ህገ ወጥ ስደተኛ አለ ተብሏል ፣ 50 ያልሞና ስደተኛ ብቻ ወደ ሀገር ቤት መግባቱን እየሰማን ነው ፣ ለመግባት ሰነድ በመውሰድ የተመገበው ዜጋ 100 ሽህ አልደረሰም ። ተዘገቦ ቲኬት በማጣት ፣ ካርጎ በመዘጋቱ ካርጎ እቃውን ለማስገባት ላይ ታች ሲል የባጀው ዜጋ በመጨረሻው ሰአት ወደ ሀገር መግባት ቢገልግም እንግልት ሆኖበታል ። ዋንኛ ምክንያቱ ደግሞ የአየር ቲኬት መታጣት ነው ። የኢትዮጵያ መንግስት ተወካዮች እንደ ጅዳ ቆንስል መረጃ ከሆነ ለተመላሽ ዜጎቻቻችን ተጨማሪ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን በሳውዲ መንግስት እንዳልተፈቀደ ጠቁሟል። ለተፈጠረው መጉላላትም ቆንስሉ ይቅርታ ጠይቋል !

የጅዳ ቆንስል ሰራተኞች ልክ የዛሬ ሳምንት በሺሜሲ አሻራ መስጫ ስራቸውን ማቆማቸው ይጠቀሳል ። ኮሚኒቲውም እያስከፈለው የሚያቀርበውን ግልጋሎት ማቋረጡን ያለ በቂ ምክንያት አስታውቋል ። ከዚያ ቀን ወዲህ በጣት አሻራ መስጫው ቀንና ሌሊት የሚንገላራው ሰው ደራሽ አልነበረውም ። ለጣት አሻራ ለማድረግ ወደ ሽሜሲ የተጓዘውን ተመላሽ ዜጋ አሻራ ለማድረግ ቀንና ሌሊት እየተንገላታ ነው ። ጉልበተኞች ተሳክቶላቸው ደካሞች ተሰላችተው አሻራ ሳያደርጉ እየተመለሱ ነው ። የአሻራ መስጫው የመጨረሻ ቀን ነገ ሀሙስ ሰኔ 15 ነው ተብሏል። ቀኑ አንዳያልፍባቸው አሁንም በርካቶች የሌቱን ወበቅ የቀኑን የበርሃ ሀሩር ከጾሙ ጋር ተቋቁመው አሻራ ለመስጠት እየታገሉ ነው ። አሻራ የሰጡት ፈግሞ ቲኬት አጥተው በአየር መንገዱ ቢሮ በር ሳይቀር ተኝተው ማደራቸውን ሰምቻለሁ ።

በዚህ ሁሉ መካከል ተስፋ ስደተኛ የሳውዲዎች እረፍት ሲራዘም የእሱ የተስፈኛው ስደተኛ እረፍት የሚጀምርበትን ቀን በጉጉት እየጠበቀ ነው ። አንድም አሻራ ሰጥቶና ቲኬት ገዝቶ መጓዝ ፣ አለያም የመጣው ይምጣ ብሎ እየጠበቀ ብቻ አይመስለኝም። … ስደት ክፉ ተስፈኛ ያደርጋል ፣ እናም ” ቸር ያሰማን” እልን ንጉሱ ያወጡታል ብለን የምንገምተውን አዳዲስ መመሪያ ፣ መግለጫም ሆነ አዋጅ በአየር ላይ ግምታችን ቸረፈስን በማሳደግ ላይ ነን … ጆሯችን አቅንተንም የተራዘመውን እረፍት ሳይሆን ከስጋት የሚያያወጣንን የሰው ልጅ የተስፋ ቃል በመጠባበቅ ላይ ነን !

ዳሩ ግን ብልጥ ከሆነንን የሰውን ተስፋ ትተን ደካሞች ነንና ወደ አንድዬ ተስፋ አንደበታችን ለምስጋና እናቅናው ! ቅዱስ መጽሐፉ ማቴዎስ በምዕራፍ 11 ቁጥር 28 ” እናንተ ደካሞች፤ ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፣ ወደ እኔ ኑ፣ እኔም አሳርፋችኋለሁ።” ብሎ ሊያድነን እንጅ ላያጠፋን ቃል ኪዳን የገባልንን አምላክ መማለድ ይበጃል ፣ እነሆ በየሐይማኖታችን በጸሎት እንጽና !

ቸር ያሰማንም እንላለን !

ነቢዩ ሲራክ
ሰኔ 14 ቀን 2009 ዓም

Image may contain: 3 people, people smiling
Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 7 years ago on June 21, 2017
  • By:
  • Last Modified: June 21, 2017 @ 10:43 am
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar