www.maledatimes.com የኤፈርት ዳሪክተር ኣዜብ መስፍን ማጭበርበር ከትግራይ ህዘብ አይሰወርም - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

የኤፈርት ዳሪክተር ኣዜብ መስፍን ማጭበርበር ከትግራይ ህዘብ አይሰወርም

By   /   June 20, 2017  /   Comments Off on የኤፈርት ዳሪክተር ኣዜብ መስፍን ማጭበርበር ከትግራይ ህዘብ አይሰወርም

    Print       Email
0 0
Read Time:9 Minute, 38 Second


——————————————————-
ባለፉት ቀናት ኣዜብ መስፍን ከዓይጋ ፎሮም ዌቭ ሳይት ጋር የኤፈርት ኩባንያዎች ማለት እንድስትሪዎች ፣ባንኮች ፣እንሽራንሾች ፣ የትራንስፓርትና ኮንስትራክሽን ኮፓንያዎች ፣ የንግድ ማእከላት ፣ የላኪና ኣሰመጭ ኩባንያዎች በሚመለከት ሁኔታቸው ለማወቅ ቃለመጠየቅ ሲደረግላት በጥሞና ሰምቸውኣለሁ።
ኣዜብ ለቀረበላት ጥያቄ የሰጠችው መልስ ከዛ በፊት ከነበሩት የኤፈርት ዳሪክቶሮች ስብሃት ነጋ ፣ ስዩም መስፍን ፣ ኣባዲ ዞሞ ልዩነቱ የነዛ የተራቀቀ ማጭበርበር ፣የኣዜብ መስፍን ያልበሰለ ግለጽ ማጭበርበር ነው የሚለያቸው ። በተረፈ የማጭበርበር ስልታቸው የኣንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታ ነው ።

የነዛ ተንኮልና ማጭበርበር በኤፈርት ሃብት በለጸገ በላ ጠጣ ሃብታም ሆነ እተባለ 25 ኣመት መሉ የተነገደለት የትግራይ ህዝብ በተለይ በቅርብ በኣጠቃላይ ደግሞ የኢትዮጱያ ህዝብ እያወቀውና እየተቸው እየተቃወሞው ኖሮዋል ኣሁንም ተቃውሞው ኣልበረደም ።

ወደ ኣዜብ መስፍን ማጭበርበርና ሽወዳ ልግባ ፣
አዜብ ኤፈርት የማን ነው ተብላ ስትጠዬቅ የሰጠቹ መልስ ፣
** ኤፈርት የማንም እጅ ጣልቃ ሳይገባበት የትግራይ ህዝብ ነው ኣለች ። ይህ ኣባባል 25 ኣመት ሙሉ ኣደንዝዞን ነረዋል ። ኣዜብ መስፍን ህዝብ በየተኛው የባለቤትነት መብት ነው የህዝብ ነው የምትለን ያለች ? እነዚህ ኩባንያዎች ከመጀመሪያ ጀምረው በባለ ቤትነት የተመዘገቡ 32 የህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ እና 4 የህወሓት ነባር ኣባላት የነበሩ በሽምግልና ኣእሙሯቸው የተዛቡ የትምህርት ቀለም ያልቆጠሩ ሁለት ከሽሬ ኣንድ ከኣድዋ ኣንድ ከእንደርታ ነበሩ ። ለምሳሌ ለመጥቀስ ወይዘሮ ነጅያ የተባሉ በዛን ወቅት ከ87 ኣመት እድሜ በላይ ነበሩ ።እኒህ እናት ልጆቻቸው በትግሉ ያለፉ ኣይናቸው ጭራሽ የደከሙ መስማት የተሳናቸው ነበሩ ።
እኒ ኣራት ሰዎች ወደዛ የባለቤትነት መብት ሲገቡ ሆን ተብሎ የህዝብ ነው ብሎ ለመጭበርበር ታሳቢ በማድረግ የተሰራ ነበር ።
ለዚሁ መራጋገጫ 32 ማ /ኮቴና ኣራቱ ኣርሶ ኣደሮች 36ቱ ማለት ነው እያንዳንዳቸው 500 ሚሊዮን ብር ሸር ተመዝገበው ሲያበቁ ፣እነዛ 4ቱ ኣርሶ ኣደሮች የተባሉት እኛ ሽማግሌዎች ስለሆን ለህወሓት ማ / ኮሚቴ ኣውርሰናል ብለው እንዲፈሩሙ ተደረገ ። ይህ ማጨበርበር ኣደለም ?
ሌላስ የትግራይ ህዝብ ለባለ ኣደራ ቦርድ በውክልና ሰጥቷል ብላለች ። መቸ ቀን ? በየተኛው ጉባኤ ? የተወከሉ እነማን ናቸው ? ለመሆኑ ከ5 ሚሊዮን የትግራይ ህዝብ ለምስክርነት የሚቀርብ ኣለን ? ሌላ ቀርቶ የህሓት ታማኝ ካድሬ የሚመሰክር ኣለ ? መልሱ የለም ነው ። ኤፈርት ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ የሸር ባለቤቶች ማ /ኮሚቴ ህወሓት ፣ቦርድ ዳሪክቶሮች ፖሊት ቢሮ ( ስራ ኣስፈጻሚዎች) ናቸው ። እስከኣሁንም የትግራይ ህዝብ ስለኤፈርት ምንም ግንዛቤም ተጠቃሚም ኣይደለም ። ኣሁን ሲመረው በተለይ ሙሁራን ተማሪዎች ወጣቶች ስለ የህወሓት ሸፍጥ በጥልቀት
እየተረዱ ሲሄዱ ጥያቄ ማንሳት ጀምረዋል ።
+++ አይጋ ፈሮም የኤፈርት ኩባንያዎች ሲጀምሩ የካፒታላቸው ምንጭ ከየትነው ሲላት ? በትግል ጊዜ ከሰተሰበሰበውና ከባንክ ብድር ነው ኣለች ። እዚህ ላይ ለጦርነት ማስፈጸምያ ተብሎ የተሰበሰበ ገንዘብ በብር ዶላር ፣ፓውንድ ፣ ደችማርክ ፣ የሱኡዲ ሩያል ፣ ነዳጅ ፣መድሃኒት ፣ የመኪና መለዋወጫ ወዘተ በቡዙ ቢሊዮን ነበረ ። እኔም በወቅቱ ስንቅና ትጥቅ ትራንስፓር ሃላፊ ስለነበርኩ በሚገባ ኣውቃለሁ ።
እኔ የማልቀበለው ከባንክ ተበድረናል ለሚለው በምክንያት ኣድርገው ለዛቁት ዶሏር ለመመዝበር ይመቻቸው ዘንዳ ሽፋን ሊሆናቸው የተሰራ ድራማ ነው እንጅ ለሁሉም ለተቋቋሙ ኩባንያዎች ማቋቋምያ በቢሊዮን የሚቆጠር ዶሏርና ፓውንድ ነበር ።ብር ቢሆን በወቅቱ ከነበረ የመንግስት ገንዘብ የበለጠ ነበር ። ያከባንኪ ተበድረናል የሚል ድራማ ለወደፊት ዶሏር ለመመዝበር ኣርቀው በማሰብ የተሰራ ድራማ ነበር ። ምክንያቱም የኩባንያዎች ትርፍ የት ገባ ለሚል ጥያቄ ኣፍ መዝጊያ ብለው ኣዛጋጅተውት የቆዩ ነው ። በዛ የስርቆት እስትራተጃቸው መሰረት ደግሞ 25 ኣመት ሙሉ ለቀረበላቸው ጥያቄ ለማጭበርበር ተጠቅመውበታል ።
ሌላ ኣዜብ መስፍን ስትሸውድ ኤፈርት የገባሬሰናይ ስራ ይሰራል በመሆኑም ለኣካል ጉዳቶኞች ፣ ለታጋይ ቤቶሰዎች አግዘናል በዘለቄታም ለ12 000 ለተሰው ታጋዮች ቤተሰብ ኣግዘናል ፣ እናግዛለን በተጨማሪም በማህበራዊ ኣገልግሎት 12 ሁለተኛ ደረጃ ት /ቤቶች ኣሰርተናል ለገናም እና ሰራለን ኣለች ።

ኣዎን እኔም የምመሰክረው በዋጅራት ፣መሶቦ ፣ሳምረ ፣ኣግበ ፣ ኣጽቢ እያንዳቸው ከ17 ሚሊዮን በላይ ብር የፈጁ ወደ 90 ሚሊዮን ብር ጨርሰዋል ። በመቀሌ ሀጸይየውሀንስ ትቤት 70 ሚሊዮን ብር ወጭ ኣድርገው ሰርተዋል ። መቀሌ እና ኣዲስ ኣበባ የሚገኜው የኣካል ጉዳቶኞች ህንጻዎች በመቀሌ 80 ሚሊዮን ብር ፣በአዲስ ኣበባ 100 ሚሊዮን ብር በድምር 370 ሚሊዮን ብር ሰጥተዋል ። ለኣካል ጉዳቶኞች ለተሰው ታጋዮች ቤተሰዎች ኣግዘናል ለምትለው ኣምና ብቻ የትግራይ ህዝብ ስለጠላቸው ወደሁሉ ስራ ኣንሳተፍም ኣንሰበሰብ ብሎ ሲተፋቸው ለመላሳለስ ተብሎ ለ10 000 የ
ሰው የታጋዮች ወላጆች ድጋፍ ማማለጃ ተብሎ 30 ሚሊዮን ብር ለአንድ ሰው ለኣንድ ጊዜ ብቻ የተሰጠ 3000 ብር ሰጠናል ብለው ነበር ከዛበኃላ ኣልቀጠሉበትም። የተሰጠው ግን ለ10 000 ሰዎች ሳይሆን ለ7000 ሰዎች ብቻ ነው የተሰጠ ለዛው ያለውና የለለው(የመነጠ) የመነጠ ወይ ባዶ የሆነ እየተባለ ልዩነት የተፈጸመ ህዝብ ያጣላ ። አንድ ላም አንድ በሬ ወይ ኣንድ ፍየል ያለው አይሰጥም በማለት ተከልክለዋል ።በትግራይ ግን ቤተሰቦቻቸው ኣባቱ እናቱ ሚስቱ ለጆቹ ጨምሮ የታጋዮች የምልሻ የገጠር ካድሬና አደራጅ ፣ አስተዳዳሪዎች የነበሩ የተሰው ቤተሰዎች የደኸዩ ከ1000 000 በላይ ወገኖች ኣሉ ። በጠሩነቱ ባሎቻቸው ፣ ልጆቻቸው ከህወሓት ጋር ተሰልፈው መስዋእቲ የከፈሉ ከሰሜን ጎንደር ከሰሜን ወሎ የላስታን የሰቆጣ ኣገው ፣ ከሰሜን ሽዋ ፣ከኣፋር
ኣይጨምርም ። ኣዜብ መስፍን ስትዋሽ ግን ለ12 000 የታጋዮች ቤተሰዎች ቀጣይ በሆነ በየወሩ እርዳታ እየሰጠን እየጦርናቸው ነን ብላለች ።

*** ኤፈርት ግን በ2008 ዓ ም ከሱር ኮንስትራክሽን ፣መስፍን እንጅነር ፣ትራንስ ኢትየጱያ ፣ከሰሚንቶ ፋብሪካ በኣመታዊ ግምገማቸው በሃወልት ሰማኣታት ያቀረበቹ ሪፖርት የኣራቱ ኩባንያዎች ብቻ 8 . 6 ቢሊዮን ከወጭ ቀሪ ትርፊ በኣንድ ኣመት እንደ ተገኜ ፣ ኣስታውቃ ለሰራቶኞች በቦኖስ በገፍ ሰጥታ ነበር ።

በ2009 ዓ ም ኣሁንም የኣራቱ ኩባንያዎች የኣመቱ ሽያጭ 27 ቢሊየዮን ሆኖ ። የተጣራ ትርፍ 11 . 4 ቢሊዮን ትርፍ እንደተገኜ ከውስጧ ታማኝ ምንጮች ተናግረዋል እንደበፊቱ እንዳያውጁት የኢትዮጱያ ህዝብ በተለይ ደግሞ የትግራይ ህዝብ እንዳያውቀው ስለሰጉ ነው ።ይህ ሁሉ ትርፊ ሌሎች 28 ኩባንያዎችን ኣይጨምርም ። ታድያ ኣዜብ መስፍን 370 ሚሊዮን እርዳታ ሰጠናል ብላ ስታጭበረብር ኣታፍርም 370 ሚሌን ብር እኮ ለኣዜብ መስፍንና ልጆቻ የኣንድ ወር የመዝናኛ ወጭ ኣትሸፍንም ። በኣንድ ወቅት እኮ በውጭ ሚድያዎች እንደሰማነው መለስ ከመሞቱ በፊት በቡዙ ሚሊዮን ዶሏር የሚቆጠር በሁለት ትላልቅ ሻንጣዎች ሞልታ ይዛ ሎንደን ኣውሮፕላን ማረፍያ ተይዛ ነበር በመለስ ድጋፍ ወይ ከውስጥ የመጡ መረጃዎች እንደ ተናገሩት መለስ ከቶኒቢለር ተነጋግሮ ነው የተለቀቀች ወይ የዳነቹ ። ጥሩ ኣዜብ ባለቹ እንቀበላትና የ20 ኣመት ትርፍ የት ገባ የትግራይ ህዝብ እኮ ታጋሽ ሆኖዋል እንጂ ከናንተ በላይ ኣልፎ ሄደዋል ።ኣሁን ግን ትእግስቱ ሟጥጦ ጨርሰዋል ። ወገኖቼ ያትርፍ 28 ኩባንያዎች ኣይጨምርም ስላችሁ ቅርንጫፎችን ኣይጨምር ። ለምሳሌ ወጋገን ባንክ ፣ኣፍሪካ ኢንሽራንስ ፣ ጉና ፣ ሜጋ ህትመት ፣ በሀገር ደረጃ ተሰማርተው የሚሰሩ ናቸው ።

*** የኣዜብ መስፍን የኤፈርት ድርጅቶች የገባሬሰናይ የህዝብ ፣ የኣካል ጉዳተኞች ናቸው ብላ ማጭበርበር ቦሷ ብቻ የተጀመረ ሽወዳ ኣልነበረም ባለፉት 25 አመታት በትግራይ ህዝብ በኣስተማሪዎች ፣በዩንቨርሲቲዎች ፣ነዋሪ ህዝብ ፣ተቃዋሚ ፓርቲዎች በፓርላማ ፣በምርጫ ወድድር ስለኤፈርት የባለቤትነት ጉዳይ የህጋውነት ጉዳይ ጥያቄ ኣንስተው የህሓት ማ/ ኮሚቴ እነ ስብሀት ነጋ ኣባይ ጸሃዬ ፣ኣርከበ እቁባይ ፣ ኣለም ሰገድ ገኣምላክ ጸጋይ በርኸ መለስ ዜናዊ ፣ወዘተ ልክ እንደ ኣዜብ እየዋሹ ነው የነሩ ።
*** እነዚህ ሰዎች ሲዋሹ ለነገ እንኳን ኣይሉም ለመድረካ ማላቀቅያ ብቻ ትሁን ምን ግዳቸው ። በዛን ጊዜ ጥያቄ ሲመልሱ ኤፈርት የኣካል ጉዳቶኞች ነው ይሉ ነበር ።
እኒህ ሰዎች ይቅርና ኤፈርት ሊሰጡዋቸውስ በነሱ ስም የተቋቋመው በመቀሌና አዲስ ኣበባ የተሰራው ሰማይ ጠቀስ ህንጻ በየወሩ በሚሊዮኖች ብር የሚቆጠር ኪራይ የሚያስገባ ፣ ትልቅ የደረቅና ፈሳሽ መጓጓዣ ኩባንያ የበዙ መኪና በስሙ በባለቤትነት የሚነገድበት ፣ የከፍት ርቢ የውሃ መጣርያ ፋብሪካ ወዘተ ኣላቸው እነዚ ኩባንያዎች ኣካል ጉዳተኞች ከመጤፍም ኣይጠቀሙበትም ። በኣሁኑ ጊዜ የትግራይ የጦርነት ኣል ጉዳቶኞች ከ126 000 ውስጥ ትንሽ የጥሮታ ኣበል የምትሰጣቸው 4600 ሰዎች ብቻ ናቸው ። ኣብዛኞቹ በልመና ተሰማርተው የሚኖሩ ናቸው ። እነዚህ ሰዎች ታመው ህክምና ኣያገኙም እነ ኣዜብ መስፍን ግን ጉንፋን ይዙዋቸው በፈለጉት አገር ሚሊዮኖች ዶሏር ይከፈላቸዋል ።
*** ኣሁን ያለው የፓርቲዎች መቋቋምያ ህገመንግስትና ከዛ የመነጨ የፓርቲዎች መቋቋምያ ኣዋጅ ሲተነትን ፣ማንም ፓርቲ የኢህኣደግ ፓርቲም ጭምር 1ኛ በቀጥታ ይሁን በተዘዋዋሪ የንግድና የእንድስትሪ ስራ አይሰራም 2ኛ ማንም ፓርቲ የራሱ ሬድዮጣብያ ተለብዥን ኣይኖረውንም ። ከምልሳን የሚጠቀምበት መጽሄት ጋዜጣ ብቻ ይኖረዋል ይላል ።

ይህ በኣእላፍ የህዝቦች መስዋእት የጸደቀ ህገመንግስት በህወሓት መሪዎች ተንዷል ኣጋሮቹ ወይ ስሪቱ የሆኑ ፓርቲዎቹም ጭምር ንደውታል ።
ታድያ ኣዜብ መስ የኤፈርት ኩባንያዎች
የሀገራችን ህገመንግስት ኣክብረው የሚነግዱ ፣በሃገራችን ካሉ ባለሃብቶች እንደኛ ግብር የሚከፍል እንደ ኤፈርት የለም ብላ ስትናገር ለማያውቃቸው ሃቅ ይመስለዋል ።

ሚድያው ለኣዜብ መስፍን ሲጠይቃት የኤፈርት ኩባንያዎች በሃገሪቱ ያለው ባለሃብት ሊሰራው የሚችል እያለ ኤፈርት ግን በጥቃቅን ንግድ እየተሰማራችሁ ለድህነት ዳርጋችሁቷል ? ብሏታል ።
የኣዜብ መልስ በጠራራ ጸሃይ ስትዋሽ እኛ የተሰማራነው በሃገር ባለሃፍት ሊሰራው በማይችል እየሰራን ለሱ ለመደገፍ ነው የምንሰራ ያለን ኣለች ።

*** ሃቁ ግን እንገራቹሁ የህትመት ስራ ኣንስተኛ ኩባንያ ነው። በኢትዮጱያ በደርዘኖች የሚቆጠሩ ማተምያ ቤቶች ኣሉ ።በመቀሌ ብቻ ብንወስድ 10 ትላልቅ ማተሚያዎች ከ20 በላይ ትናንሽ ኣሉ ።ግን የመንግስት ስራ በሃገር ደረጃ የሚሰጠው ለሜጋ ህትመትና ኣሳታሚ ድርጅት ነው ። በመቀሌ ያሉ ማተምያቤቶች እየዘጉና እሸጡ ወደሌላ ክልሎች ሄደዋል ።ሌሎችም የሚገዛቸው ኣጥተዋል እንጅ ከስረዋል ። ትናንሾችም እየሞቱ ናቸው ።

*** መሰፍን እንጅነር ብንመለከትስ ፣ ከመስፍን መመስረቱ በፊት መኪና የሚገጣጥም የኤረክሽ ወይ ፋብሪካዎች የመገጣጠም ስራ የሚሰራ መቀሌ ለመጀመሪያ ጊዜ ከ5000 ስኬር ሜትር ወይ ግማሽ ሄክታር መሬት ወስዶ በቡዙ ሚሊዮን ብር ወጭ በማድረግ እጅግ ዘመናዊ ዎርክ ሾብ ሰርቶ ስራ የጀመረ ፣ለመስፍን ለሌሎች ባለሃብቶች ያስተማረ ማሩ ተፈራ ነበር ያሁሉ ሃብት ወጭ ኣድርጎ ለመስፍን ያስተማረ ከመቀሌ ተባርሯል ሌሎች ትናንሽ የብረታ ብረት ስራ ፣ኤረክሽን የጀመሩም በመስፍን እንጅነር ተገፍተው እንዲወጡ ተደረጉ ። እንዲዋጡም ተደርገዋል ።የተራ የብረት መዝግያ ስራም በመስፍን ተይዞ ነበር ፣ የትግራይ ባለሃብቶች ሲጨንካቸው ማሩ ተፈራ ተከትለው ኣዲስ ኣበባ ደቡብ ሱዳን ሄደዋል ። ከነሱ ከሸሹ ውስጥ እነ ኣብይ ሃይሉ ፣ኣሸናፊ ሃይሉም ይጠቀሳሉ ።

*** ጉናስ ፣ ጉና በሙሉ የንግድ ስራ በሁሉም በኢትዮጱያ ክልል ያሉ ነጋዴዎች ሊሰሩት የሚችሉ ፣የላኪና ኣስመጭ ፣የችርቻሮ የጅምላ ንግድ ስራ በሞኖፓል በመያዝ በተለይ የሰሚንቶ ለከንስትራክሽን የሚያስልጉ ግብኣቶች ሁሉም ኣይነት ብረታብረት ቆርቆሮ ፣ HRS ፣ ሽኮር ጨው ፣ ወ ዘ ተ በሞኖፓል በመያዝ ፣ቡዙ ነጋዴ ኣፈናቅለዋለ በተለይ በጣም የወረደ የስስታም ስራ ከመሰቦ ስሚንቶ ፍብሪካ ማንም ነጋዴና ነዋሪ ህዝብ በቀጥታ ሊወስድ የሚገባው ስሚንቶ ለጉና ይሰጣልና ህዝቡና ኣከፋፋይ ነጋዴና ቸርቻሪ ለጉና ትርፍ ኣስገኝቶ ከጉና ይገዛል ።

*** ትራንስ ኢትዮጱያ የደረቅና የፈሳሽ ጭነት መማላለሻ ኩባንያም እንደሌሎች እህት ኩባንያዎች የሀገራችን ያገር ውስጥና ከውጭ ወደ ኣገር የሚገባ ሁሉም ኣይነት ጭነት የመንግስት ፣ የፓርቲ ኩባንያዎች ፣ የእርዳታ ጭነት ኣብዛኛው ጭነት ያለጨረታ በስምምነት በተጽእኖ ለትራንስ ይሰጠዋል ለዛው የእርዳታ ድርጅቶች የሚከፈለው በዶሏርና በፓውንድ ነው ወይ በከናዳ ዶላርና በደችማርክ ነው ። ሌሎች የግል የነጥረት ፣ የድንሾ እኩሉ ከትራንስ ኢትየጱያ የማጓጓዝ ኣቅም ቢኖራቸው የትራንስ ጌታ ኣዳሪነት ሳብ ኮንትራት ሆነው ኮምሽን እተቆረጠባቸው የሚሰሩ ናቸው ።
በኣጠቃላይ በኢትዮጱያ ያሉ ግለሰዎች በማህበር ተደራጅተው የትራንስ ኢትየጱያ እጥ ፍ
እጥፍ መኪኖች ቢኖሩዋቸውም የትራንስ ጥገኛ ሆነው መስራት የግድ የሏቸዋል ። ትራንስ ኢትየጱያ ሌላ ቀርቶ በክልሎች ያሉ ዞኖች ወረዳዎች ለሚደረግ መጓጓዣ ለትራንስ ኢትዮጱያ ነው የሚሰጠው።ለዚሁ ሀቅ በሀገራችን ያሉ የትራንስፓር ማህባራት ኩባንያዎችይመስክሩ በተለይ ደግሞ በመቀሌ የሚገኜው ሰላም የደረቅና የፈሳሽ ኩባንያ ማህበር ሊመሰክር ይችላል ።ኣባሎቹ መኪና የገዙበት የባንክ እዳ መክፈል ተስናቸው ከስረው እያለቀሱ ይኖሯለ ።

*** ሱር ኮንስትራክሽን ቢሆን ባገራችን ያለው የመሰረተልማት ስራዎች ኣብዛኛው ያለጨረታ በድርድር ይሰጠዋል ።ቡዙ ኣገር በቀል የኮንስትራክሽን ኩባንያዎች ከደረጃ ኣንድ እስከ ደረጃ ስምንት የስራ ፍቃድ ያላቸው ኮንትራክቶሮች እያሉ ። በደረጃ 5 እና 6 ገብቶ በመስራት ኣገር በቀል ኮንትራክተሮች እንዳያድጉ ወይ እንዲሞቱ ኣድርጓል ። ከሱ ጋር እኩል ደረጃ ያላቸው ኩባንያዎች ስራ የሚሰጣቸው ሱር ኮንስትራክሽ በቃኝ ካለ በኃላ ነው ስራ የሚሰጣቸው ።

*** የቀሩት 28 ግዙፍ ኩባንያዎችም በሙሉ በሌሎች ኣገር በቀል ኩባንያዎች ሊሰሩ እየቻሉ ስለህዝብ ተጠቃሚነት ደንታ የሌለው የህወሓት ኣማራር ግን አዜብ መስፍን እንዳለቹ ለባለሀብቶች የሚያሰለጥንና የሚደግፍ ሳይሆን የህወሓት ተላላኪ ያልሆኑ ባለሃብቶች ሆን ብሎ እንዲነቀሉ ነው እየተንቀሳቀሰ የቆየው ኣሁንም እየተገበረው ያለው ። የመለስ ረኣይ እኮ በሀገራችን ያሉ የንግድ እና የእንድስትሪ የእንጅነሪንግ ኩባንያዎች ከ10 ኣመት በኃላ 100% በኢህኣደግ ኣባል ፓርቲዎችና በመከላከያ ምኒስቴር ፣ ስር እንደሚሆን በግልጽ ኣስሙሮበት ኣልፈዋል ።ታድያ ኣዜብ መስፍን የምታዳናግረው እንዴት ብሎ ተቀባይነት ያገኛል ። እነዚህ ፍጡራን በበረሃ ኣለም የደረሰበት ስልጣኔ እንዳናውቅ ኣፍነውን የኖሩ ኣልበቃም ብሉዋቸው አሁንም ለዚሁ ኣዲስ ትውልድ አጭበርበረው ሊያልፉ ነው የሚፈልጉ ? ፍጹም ኣይሆንም ። ኣይቻልንም ።

*** ጠያቂው ለኣዜብ መስፍን ኤፈርት ግልጽነተ ይጎድለዋል ፣የኤፈርት ሃብት ኦዲት ኣይደረገም ብሎ ሲጠይቃት ?
ኣዜብ ኣይኑ ያፈጠጠ ውሼት ስትዋሽ ፣ሁሉም ኩባንያዎች የውስጥና የውጭ ሂሳብ የሚደርጉ ኣሉ ።የመንግስት ፋይናንስም ኦዲት ያደርጋሉ ብላ ዋሸች ።
ዋዋዋ ለኣዜብ እና ለህወሓት ኣማራር ህዝብ እንዲያውቃቸው የማውቀው እመሰክርላችሁ ኣለሁ ።
ኤፈርት ሲመሰረት ስልጣኑ በህወሓት እጅ በመሆኑ ኣብዛኞቹ ኩባንያዎች መዋቅራቸው ለስርቆትና ለማጭበርበር በሚመች ስለተዋቀሩ
ገቢና ወጭውም ለኦዲት በማይመች መልኩ ነው የተዋቀረው ።

ከ8 ኣመት በፊት በኢፈርት ደረጃ ተጠሪነቱ ለነስብሃት ነጋ የሆነ በኦዲተርነት ከፍተኛ ሙያ ያላቸው ምርጥ እዲተሮች ቀጥሮ የሁሉም የኤፈርት ኩባንያዎች የገቢና ወጭ ሰነዶች ወደ ኤፈርት እየተሰበሰበ ኦዲት ይደረግ ተብሎ ነበር ። ሙሁራኑ የኤፈርት ኣሰራር እጅጉን የተዝረከረከ ስለነበር ፣ ኦዲቶሮች ቡዙ ሃብት ገንዘብ እንደተጠፋፋ እና ወደ ህግ የሚያቀርብ ትልቅ ጉድለት እንዳለው ሪፓርት በማቅረባቸው ፣ እነዛ ቦርድ ዳሪክቶሮች ለኦዲተሮቹ ተጠፋፋ የምትሉት ሃብት ሰርዙት ብለዋቸው ፣ ኦዲቶሮችም ለሙያቸው የሚጻረር ኣሰራር በመሆኑ ኣመታት የጨረሰ የእዲት ስራ መሰረዝ ሂሊናቸው ስላልፈቀደላቸው ከሰራቸው በነስብሃት ነጋ ተገፍተው ተባረሩ ።
ስለዚህ ኣዜብ መስፍን እንደዚህ ኣይነት ኣሰራር የሚከተል ኤፈርት
በጥራት ኦዲት ይደረጋል ብላ ስትናገር ማን ይቀበላታል ?? ።

*** ኣዜብ በቢሊዮን የሚገመት የኢፈርት ብር የት ገባ በማን ቁጥጥርስ ይተዳደራል ሲላት ፣ ለመዋሼት ድንብርጭ የማይላት ኣዜብ ኤፈርት እስከኣሁን የተገኜ ገቢ ለባንክ እዳ ከፈልነው ኣለች ።

የተከበራቹ ኣንባብያን ኣዜብ ቀደም ሲል የኤፈርት ኩባንያዎች የተመሰረትበት ለጦርነት ማስፈጸምያ ተብሎ የተሰበሰበ ገንዘብ ጦርኖቱ ከተቃጨ በኃላ የቀረው በጦርነት ለተጎሳቆለውን የትግራይ ህዝብ ማቋቋማ የሚያክል ቡዙ ገንዝብ ነበረን ብላለች።
እኔም ጦርኖቱ ካለቀ በኃላ በወቅቱ እጅግ ቡዙ ቢሊዮን ብርና ዶላር ፓውንድ ፣ ወርቅ ነበር ። እንዲሁም ዋጋው በቢልዩን ብር የሚቆጠር የተሸጠ መድሃኒት ፣ የምግብ ዘይት ፣ ሽኮር ፣ ነዳጅ የሞተር ፣ዘይት ፣ የተሽከርካሪዎች መቀያየሪ እቃ ፣ ተሸከርካሪዎች ፣ ሌሎች ቁሳቁስ ተሽጠው ቡዙ ቢሌን ብር ነበር ፣ በሱኡዲ ኣረብያ ፣በኢጣልያን ፣ በእንግሊዝ የንግድ ኩባንያዎች ነበሩ ። እነሱም ቡዙ ገንዘብ ነበሩ ይህ ሃቅ እኔ የስንቅና ትጥቅ የትራንስፖርት ስልጣን ስለነበረችን የነበረን የገንዘብ መጠን በሚገባ ኣውቃለሁ ። በወቅቱ የኤፈርት የባለቤትነት ጉዳይ በመቃወም
እስከ በነፍጥ መማዘዝ ደርሸ ነበር ። በመሆኑ ኣዜብ የምትለው ያለች ሁሉ ለትግራይ ህዝብ ማታለል ነው ።

ኣዜብ መስፍን ብድር ነበረን ስትለን ግን የህወሓት ኣማራር ለረጅም ጊዜ የሚሰራ ያስቀመጡት የሸፍጥ እስትራተጂ ለመሸፈን ብላ እያታለለችን ያለች መሆኗ ነው ።

የኣዜብ ስለኤፈርት የባለ ቤትነት ጉዳይ ሌሎች የሸፍጥ ዘዴዎች የተናገረቹ መልስና ኣስተያየት እየቆራረጥኩ እቀጥልበት ኣለሁ ለዛሬ እዚሁ ላብቃ
ከኣስገደ ገብረስላሴ ወሚካኤል ፣
በ13 / 10 2009 ዓ ም

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 7 years ago on June 20, 2017
  • By:
  • Last Modified: June 20, 2017 @ 9:06 pm
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar