Read Time:37 Second

by Muluken Tesfaw
በምዕራብ ጎጃምና አዊ ዞኖች የገበሬውን ሀብት ንብረት የሚያወድም አደገኛ አንበጣ ተከስቷል፡፡ አንዱ የአንበጣ መንጋ በቀን 16 ኪሎ ሜትሮችን መጓዝ የሚችል ሲሆን ባሕር ዛፍን ጨምሮ ማንኛውንም ዓይነት ሰብልና እጽዋት መድምዶ በመብላት ያወድማል፡፡ በምዕራብ ጎጃምና በአዊ ዞኖች ከአራት ወረዳዎችና ከ50 በላይ ቀበሌዎች በአንበጣው መንጋ ተወረዋል፡፡
አንበጣው የሚመርጠው የለም፤ ገበሬዎች ‹‹ሁሉን በይ አንበጣ›› ይሉታል፡፡ የግብርናና የልማት ባለሙያዎች ለክልሉ መንግሥት ግብርና ቢሮ አንበጣው መጥፋት የሚችልበትን መድኃኒት ወይም ማንኛውም ዓይነት እገዛ ቢጠይቁም በአገር ውስጥ ለዚህ ዓይነት አንበጣ መከላከያ የሚሆን መድኃኒት የለም የሚል መልስ እንደተሰጠ ሰምተናል፡፡ አስቸኳይ ርብርብ ተደርጎ መከላከል ካልተቻለ በስተቀር አጠቃላይ የምዕራብ ጎጃምንና የአዊ አካባቢዎች ያለውን ሰብልና እጽዋት አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ሊያወድም ይችላል ተብሏል፡፡
እስካሁን ድረስ ባለው ከሃምሳ በላይ ቀበሌዎች በበልግ ዝናብ የበቀለ ሰብልና በአካባቢው ያለውን እጽዋት ሁሉ እንዳወደመ ለማወቅ ተችሏል፡፡
Wondering where the comments are? We encourage you to use the share buttons below and start the conversation on your own!
- Email a link to a friend (Opens in new window) Email
- Share on Facebook (Opens in new window) Facebook
- Share on X (Opens in new window) X
- Share on LinkedIn (Opens in new window) LinkedIn
- Share on Pinterest (Opens in new window) Pinterest
- Share on Tumblr (Opens in new window) Tumblr
- Print (Opens in new window) Print



Print
Email
Average Rating