www.maledatimes.com ሰበር መረጃ ፣ መካ ካዕባን የማጥቃት ሙከራው ከሸፈ ! - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

ሰበር መረጃ ፣ መካ ካዕባን የማጥቃት ሙከራው ከሸፈ !

By   /   June 23, 2017  /   Comments Off on ሰበር መረጃ ፣ መካ ካዕባን የማጥቃት ሙከራው ከሸፈ !

    Print       Email
0 0
Read Time:48 Second


* አንድ አሸባሪ ራሱን በራሱ አጥፍቷል
* 10 ሰዎች ቆስለዋል
* አንድ ሴትን ጨምሮ አምስት ተጠርጣሪዎች ተይዘዋል

የሳውዲ ደህንነት ልዩ ግብረ ኃይል በዛሬው እለት ታላቁን የመካ ካዕባ መስጅድ ለማጥቃት የተደረገ ሙከራን ማክሸፉን የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ ሜ/ጄኔራል መንሱር አልቱርኪ አስታውቀዋል ።

ከደህነት የወጣው መረጃ እንደሚያመለክተው ከሆነ ጥቃቱን ለመከዎን ሶስት ቡድኖች ሁለቱ ቡድኖች ከመካ ሶስተኛው ቡድን መሰረቱን ያደረገው ጅዳን እንደነበር ተጠቅሷል ። የመጀመሪያው ሁለተኛው የጥቃት ሙከራዎች መካ ውስጥ በተለያዬ ቦታ ተደርሶባቸው መክሸፋቸው ታውቋል ። ጥቃት ሊያደርሱ ከነበሩት አሸባሪዎች መካከል አንዱ መካ ውስጥ አጅያድ በተባለው መንደር በክትትል ተደርሶበት እጁን ለጸጥታ አስከባሪዎች እንዲሰጥ ቢጠየቅም ፈቃደኛ አልሆነም ተብሏል ።

አሸባሪው እጁን አልሰጥም በማለት በጸጥታ አስከባሪዎች ላይ ተኩስ ከፍቶ የነበረ ቢሆንም ማምለጫ ሲጠፋው ራሱን የታጠቀውን ቦምብ ራሱን በራሱ ማጥፋቱን የሀገር ውስጥ ሚኒስትር ቃል አቀባይ ተናግረዋል ። በተኩስ ልውውጡ ስድስት ያህል ሰላማዊ ሰዎችና አምስት የጸህንነት ጸጥታ አስከባሪዎች የቆሰሉ መሆኑም ታውቋል ።

ከሽብር ጥቃቱ ጋር በተያያዘ አንድ ሴትን ጭምሮ በአጠቃላይ አምስት ያህል ሰዎች በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን ምርመራ እየተካሄደባቸው መሆኑን በመገናኛ ብዙሃን የተሰራጨው መረጃ ያስረዳል ።

ቸር ያሰማን !

ነቢዩ ሲራክ
ሰኔ 16 ቀን 2009 ዓም

About Post Author

Abby

Internet reporter, freelancer and webmaster.
Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 7 years ago on June 23, 2017
  • By:
  • Last Modified: June 23, 2017 @ 3:11 pm
  • Filed Under: Ethiopia

About the author

Internet reporter, freelancer and webmaster.

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar