www.maledatimes.com (ሰበር ዜና) በአባይ ጸሐዬ ትዕዛዝ ከ እስር ተፈተው የነበሩት ወ/ሮ ሳሌም ዳግም ታሰሩ * የፖለቲካ ስልጣናቸው ጉልበት አጥቷል - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

(ሰበር ዜና) በአባይ ጸሐዬ ትዕዛዝ ከ እስር ተፈተው የነበሩት ወ/ሮ ሳሌም ዳግም ታሰሩ * የፖለቲካ ስልጣናቸው ጉልበት አጥቷል

By   /   July 29, 2017  /   Comments Off on (ሰበር ዜና) በአባይ ጸሐዬ ትዕዛዝ ከ እስር ተፈተው የነበሩት ወ/ሮ ሳሌም ዳግም ታሰሩ * የፖለቲካ ስልጣናቸው ጉልበት አጥቷል

    Print       Email
0 0
Read Time:42 Second

 


(ዘ-ሐበሻ) በትናንትናው የዘ-ሐበሻ ዘገባ የአባይ ጸሐዬ ሚስት ወ/ሮ ሳሌም ከበደ መታሰራቸውን መዘገባችን ይታወሳል:: ወ/ሮ ሳሌም ከቀድም ባለቤታቸው የወለዱትን ልጃቸውን ድረው መልሱን ሳይበሉ ዘብጥያ የወረዱ ሲሆን ባለቤታቸው አባይ ጸሐዬ የፖለቲካ ስልጣናቸውንና እርሳቸውን የሚደግፉ ሕወሓቶችን በማስተባበር ሚስታቸው እንዲፈቱ አድርገው የነበረ ቢሆንም ከሰዓታት ፍቺ በኋላ ወ/ር ሳሌም ዳግም ዘብጥያ መውረዳቸውን የዘ-ሐበሻ ምንጮች አስታውቀዋል::

የዘ-ሐበሻ ምንጮች እንደሚሉት ከሆነ በሙስና ተጠርጥረው የታሰሩት አብዛኞቹ ነጋዴዎች ከአባይ ጸሐዬ ጋር የንግድ ንክኪ ያላቸው ናቸው:: አባይ ጸሐዬ የተለያዩ ጀነራሎች ጋር በመደወል ሚስታቸውን ለማዳን ቢጥሩም እንዳልተሳካላቸውና እርሳቸውም ከተጠያቂነት እንደማያመልጡ የዘ-ሐበሻ ምንጮች አስታውቀዋል::

አባይ ጸሐዬ በሕወሓት መንግስት ውስጥ የፖለቲካ ስልጣን እንጂ ሃይል ያለው ስልጣን የለውም የሚሉት የዘ-ሐበሻ የፖለቲካ ተንታኞች ሃይል ያለው የነደብረጽዮን (ስብሃት ነጋ) ቡድን እንደሆነና ይህም የአባይ ጸሐዬን ቡድን እያሽመደመደው መሆኑን ይገልጻሉ:: በተለይም የነብርሃኔ ገብረክርስቶስ ወደ ቻይና በአምባሳደርነት መሄድ ከዚሁ በሕወሓት ውስጥ ከተፈጠረው ግብ ግብ ጋር የተያያዘ ነው ይላሉ::

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 7 years ago on July 29, 2017
  • By:
  • Last Modified: July 29, 2017 @ 5:14 pm
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar