www.maledatimes.com ጋዜጠኛና ገጣሚ ሰለሞን ደሬሳ ከዚህ አለም በሞት ተለየ - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

ጋዜጠኛና ገጣሚ ሰለሞን ደሬሳ ከዚህ አለም በሞት ተለየ

By   /   November 2, 2017  /   Comments Off on ጋዜጠኛና ገጣሚ ሰለሞን ደሬሳ ከዚህ አለም በሞት ተለየ

    Print       Email
0 0
Read Time:59 Second

ጋዜጠኛ እና ገጣሚ ሰለሞን ደሬሳ ለእረጅም ጊዜ በምንሶታ ኑሮውን አድርጎ በህክምና ባለሙያዎች ሲረዳ ቆይቶ ህይወቱ ማለፉን ከቅርብ ወዳጃችን ከቴአትር ባለሙያ ከእጩ ዶ/ር ሱራፌል ወንድሙ ለመረዳት ችለናል።

መልካም እና ቀና የነበረው ሰለሞን ደሬሳ በበሳሉ እና ጠንካራ ፅሁፎቹ የሚታወቅ የነበረ ሲሆን  በፈረንሳይኛ፣እንግሊዝኛ እና አማርኛ ፅሁፎቹ ጥሩ አድርጎ የሚፅፍ እንደነበር ዘገባዎች ይጠቁማሉ ።

ሰለሞን ደሬሳ በወለጋ አካባቢ የተወለደ ሲሆን በ80 አመቱ ህይወቱ ማለፉን የደረሰን ሪፖርት ያመለክታል።

ስርአተ ቀብሩ በቅዳሜ እለት እንደሚከናወንም ጥንቅሩ ያመላክታል ።

በበሳል እና ጠንካራ ፅሁፎቹ የሚታወቀው ሰለሞን ደሬሳ የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን በማለዳ ታይምሰ ዝግጅት ክፍል እናቀርባለን

ኒርቫና

እንዲህ ነው መነጠል
እንደዚህ ነው ማለፍ

ፀዳል ተጎናፅፎ
አክሊል ተከናንቦ …

እያበሩ መሄድ
እየበሩ መምጣት …

እንዲህ ነው ሳምሳራን
ሰንክሳሩን መስበር

ማለፍ ላለማለፍ
ላለማረፍ ማረፍ

ስለ እውነት መንቃት
በዓለም ላይ መብቃት

ዕውነት፣ ትሁት መሆን
መጠየቅ ማስተንተን …

መፍጠርና ማድነቅ
ቋሚን አለማምለክ …

ገላ ሰጋን መጣል
ሰውነትን ማንሳት

የሰው “ዚነት” ሆኖ ካ’ለም “ናዲር” መራቅ
መጓዝ በጥሞና ፀጥ ብሎ መሳቅ …

ባ’ማዲየስ ሞዛርት፣ በቤቶቨን ፈረስ
በስትራቭንስኪ፣ በባህ በብራህምስ
በሾፐን በሄንድል በቪቫልዲ መፍሰስ …

በሜሪ በአስናቅች በጂጂ ሙዚቃ
በባቲ ዜማ ግርፍ ባዝማሪዎች ጭራ
በወለሎ ቅኝት በድቤ ዝየራ …

በእስክንድር በገብሬ፣ በተስፋዬ ስብሃት
ካገርህ ተድረህ አገርክን ፈታሃት …

ከጩታ አዲሳባ፣ አልፎም እስከ ፓሪስ
ከውቤ በረሃ ቃጠሎ ካዛንቺስ
እስከ አምባ ቆራ ነጭዋ ምኒያፖሊስ …

ሰው ሆነህ ተገልጠህ
ሰው ሆነህ ተነጠልህ
ሰው ሆነህ ተመለስህ …

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar