www.maledatimes.com “6 ልጆቻቸውን ለህወሓት ትግል የገበሩ እናት ጐዳና ላይ ወድቀዋል” - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

“6 ልጆቻቸውን ለህወሓት ትግል የገበሩ እናት ጐዳና ላይ ወድቀዋል”

By   /   February 23, 2019  /   Comments Off on “6 ልጆቻቸውን ለህወሓት ትግል የገበሩ እናት ጐዳና ላይ ወድቀዋል”

    Print       Email
0 0
Read Time:1 Minute, 21 Second

“6 ልጆቻቸውን ለህወሓት ትግል የገበሩ እናት ጐዳና ላይ ወድቀዋል”

 የእውቁ የህወሓት ታጋይና የትግርኛ ዘፋኝ ብርሃኑ ጋኖ እናት በችግር ጐዳና ላይ መውጣታቸው ተጠቆመ፡፡ ወይዘሮዋ 6 ልጆቻቸውን ለህወሓት ትግል ገብረው ጧሪ ቀባሪ በማጣት፣ በአሳዛኝ ሁኔታ በመቀሌ ጐዳና ላይ መውደቃቸውንና በቅርቡ ወደ ተንቤን መሄዳቸውን ጉዳዩን በቅርበት የሚያውቁት አቶ አርአያ ተስፋማርያም ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡ 
የህወሓት ታጋዮች በወኔ ወደ ትግል እንዲገቡ ሲቀሰቅሱና ሲያነሳሱ ከነበሩት ድምፃዊያን ታጋዮች መካከል አንዱ የሆነው ብርሃኑ ጋኖ፣ ለትግሉ ከፍተኛ መስዋዕትነት የከፈለ ቢሆንም ህወሓት ወደ ስልጣን ከመጣ በኋላ እንደ ሸንኮራ ተመጥጠው ከተተፉትና ከተገፉት ታጋዮች አንዱ መሆኑን አቶ አርአያ አስታውሰዋል፡፡ 
ከስድስት አመት በፊት ከትግራይ ወደ ሱዳን የባህልና የኪነት ቡድን አሳፍሮ ይጓዝ በነበረ መኪና ላይ በደረሰ አደጋ ህይወታቸውን ካጡት ድምፃዊያን መካከል አንዱ ብርሃኑ ጋኖ ሲሆን፤ በተለይም እሱ ከሞተ በኋላ ወላጅ እናቱን የት ወደቅሽ ብሎ የሚጠይቃቸው ወዳጅ ዘመድ በማጣታቸው፣ በመቀሌ ጐዳና ላይ ለልመና ተዳርገው እንደነበር የቅርብ ምንጮቹን ጠቅሰው አቶ አርአያ ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡፡ 
የታጋዩና ድምፃዊው እናት በአሁን ሰዓት ከመቀሌ ጐዳና ወደ ተንቤን መሄዳቸውን የጠቆሙት አቶ አርአያ፤ ኩዌት የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን አዋጥተው በላኩላቸው ጥቂት ገንዘብ ህይወታቸውን ለማቆየት እየተፍጨረጨሩ እንደሆነ ተነግሯል፡፡ ብርሃኑ (ጋኖ) በተለይ በቅብብሎሽ ባቀነቀነው ዘፈኑ ብዙ በሺህ የሚቆጠሩ ወጣቶች ትግሉን እንዲቀላቀሉ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ቢያደርግም፣ ከሥርዓቱ እንኳን ሊጠቀም ጭራሽ ተገፍቶ፣ በግሉ ህይወቱን ለመምራት በትግል ላይ እያለ ነው በመኪና አደጋ ህይወቱ ያለፈው፡፡ 
የወላድ መካን የሆኑት የእነ ብርሃኑ እናት፣ ስድስት ልጆቻቸውን ለሕወሓት ትግል ገብረው ፣የማምሻ እድሜያቸው በመከራ የታጀበ መሆኑ እንደሚያም የገለፁት አቶ አርአያ፤ እኚህ እናት የበርካታ የትግል ሰለባ ልጆች እናቶች ማሳያ ናቸው ብለዋል፡፡  
ጥቂት ባለስልጣናት እስከ 10 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ቪላ ቤት ለልጆቻቸው ሳይቀር ሰርተው እየኖሩ፣ ለትግሉ መሳካት አጥንትና ደም የገበሩ ወጣቶች እናቶች ሜዳ ላይ ወድቀው መከራ ሲገፉ እንደማየት የሚያስቆጭ ነገር የለም ያሉት አቶ አርአያ፤ የብርሃኑ ጋኖን እናት የመጨረሻ የህይወት ዘመን ለማሻሻል ሰብአዊነት የሚሰማው ወገን ሁሉ ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ተማፅነዋል፡፡  

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 5 years ago on February 23, 2019
  • By:
  • Last Modified: February 23, 2019 @ 1:25 pm
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar