www.maledatimes.com ባሳለፍነው ሳምንት በቢሾፍቱ አካባቢ የተከሰከሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ተሳፋሪዎች እና ሰራተኞች ስርአተ ቀብር በስላሴ ተፈጸመ! - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

ባሳለፍነው ሳምንት በቢሾፍቱ አካባቢ የተከሰከሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ተሳፋሪዎች እና ሰራተኞች ስርአተ ቀብር በስላሴ ተፈጸመ!

By   /   March 17, 2019  /   Comments Off on ባሳለፍነው ሳምንት በቢሾፍቱ አካባቢ የተከሰከሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ተሳፋሪዎች እና ሰራተኞች ስርአተ ቀብር በስላሴ ተፈጸመ!

    Print       Email
0 0
Read Time:2 Minute, 37 Second

በዘለአለም ገብሬ

አንድ መቶ አምሳ ሰባት ተሳፋሪውቾችን አሳፍሮ ወደ ኬንያ ያቀና የነበረው አውሮፕላን በቢሾፍቱ ከስድስት ደቂቃ በረራ በኋላ መውደቁ የተነገረ በአለም ላይ አስደንጋጭ ዜና ነበር።

ሰባት ሰላሳ ሰባት ማክስ 8 -9 የተሰኙት ነዳጅ ቆጣቢ አውሮፕላኖች በውስጣቸው በሚሊዮን የሚቆጠሩ የኮምፒዩተር ፕሮግራም ወይንም ኮድ ሚስጥራዊ ቁጥር የተሞላ ዘመናዊ እና ቴክኖሎጂን ያዋቀረ አውሮፕላን መሆኑ ተነግሮለታል ፣ ይህ አውሮፕላን በፋብሪካው ተሰርቶ ከወጣ ጊዜ ጀምሮ ሁለት ግዙፍ አውሮፕላኖቹ በጣም በአጭር ጊዜያት ውስጥ መውደቃቸው እና የብዙ ዜጎች ህይወት መጥፋቱን አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ሲገልጹ መክረማቸው ይታወቃል።

Image may contain: 2 people, people standing, crowd and outdoor

በአውሮፕላኑ የመቆለፊያ ዘለበት( lock knob) ከተሰኘው ችግር ውጭ፡ብዙ የኮፕምዩተር፡ፕሮግራም፡ስህተት፡እንዳለበት፡እና፡በበረራ፡ወቅት፡በፍጥነጥ አፍጫውን ወደ ሰማይ በማሾል ወይንም ወደ መሬት በማቆልቆል እራሱን የሚወረውር ሃይል እንዳለው በተለያዩ አለም አቀፍ የመረጃ ተቋማት ሳምንቱን ሙሉ ሲዘገብ ከርሟል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከኢትዮጵያ አውሮፕላን በረራ መከስከስ በኋላ የአሜሪካው ፕረዚደንት ዶናልድ ትራምፕ በአስቸኳይ የቦይንግ 737 max 8 እና 9 ከአገልግሎታቸው እንዲቆሙ እና አስፈላጊው ምርመራ ተደርጎ ፣ ችግሮቻቸው ተፈቶ ወደ ስራ የሚመለሱበትን አስቸኳይ አዋጅ ማውጣታቸው ይታወሳል። 737 የበረራ ክልከላም መደረጉን ተደገልጿል::

በዚህ ባሳለፍነው ሳምንት ፋክስ ቢዝነስ አለም አቀፍ የዜና አውታር ስለ ቦይንግ ካምፓኒ የንግድ ክስረት ሃያ አምስት ቢሊዮን ደላርስ እንደደረሰበት የተገለጸ ሲሆን ፣ 5100 737 ማክስ 8-9 በአጭር ጊዜ መሸጣቸው የተገለጸ ሲሆን ፣ በዚህ አደጋ የስቶክ ማርኬት ኤክስቸንጅ 10% ዋጋው በአንድ ጊዜ እንደወደቀበት ፋክስ ገልጿል።

በዛሬው እለት በጋራ የተቀበሩት የአየር መንገዱ ሰራተኞች እና ተሳፋሪዎች በጸባኦት ቅድስት ስላሴ መካነ መቃብር ሲሆን ፣ የተጓዦቹን አስም በማቃጠል አመድ ለቤተሰቦቻቸው እንደተሰጠ እና ባዶ ሳጥን በማረፊያ ክፍል ውስጥ መቀመጡን አለም አቀፍ መረጃ ማእከሎች እየዘገቡት ይገኛሉ ። ብዙሃንን ያሳዘነው የዚህ አየር መንገድ በረራ አስተናጋጆች አብራርሪዎች እና እና ተጓዦች በስድስት ደቂቃ የደረሰው የእልፈተ ህይወት አደጋ ፣ ለዜጎቹ ሰቀቀን ነው ሲሉም ይደመጣሉ ። የብዙሃን የውጭ ዜጎች አስከሬን ምን እንደሚሆን ግን የተገለጸ ነገር የለም

Image may contain: one or more people

በዛሬው እለት እየሩሳሌም ፖስት የተሰኘው ጋዜጣ ደግሞ በአሳተመው ጋዜጣ ላይ እንደገለጸው ከሆነ ባለፈው ሳምንት የመከስከስ አደጋ በደረሰበት የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ህይወታቸውን ባጡት ሟቾች ላይ የተፈፀመባቸው ክብረነክ ተግባር እንዳሳዘነናቸው የእስራኤል የበጎፈቃደኞች ቡድን ለጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይና ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳውቀዋል።
የሟቾች ንብረቶች በአካባቢው ነዋሪዎች መዘረፋቸው እንዳሳዘናቸው ገልፀው፤ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚንስትር ወደ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ በመደወል ለጉዳዩ መፍትሄ እንዲሰጠው ቢጠይቁም ቀና መልስ እንዳላገኙ ታውቋል ሲል ጄሩሳሌም ፖስት ዘግቧል። ለበለጠ መረጃ ከስር ሊንኩን ይጫኑት

https://www.jpost.com/Israel-News/Israeli-volunteers-condemn-Ethiopian-governments-handling-of-plane-crash-583580?fbclid=IwAR0jLKGOi1GEo6qy0U5jvLX4QZA4T-mZOXhL1ZaYZUqqfVty4Lpo0uM93jU

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከዘሃበሻ ያገኘነው መረጃ እንደሚያመለክተው ከሆነ ለተከሰከሰው አውሮፕላን ዛሬ የሰማናቸው 5 መረጃዎች!
1. በዛሬው እለት የ17ቱ ኢትዮጵያዊያን የቀብር ስነስርአት በቅድስት ስላሴ ቤተክርስቲያን ተከናውኗል፡፡ አሶሺየትድ ፕሬስ እንደዘገበው እነዚህ 17ቱ ባዶ የአስከሬን ሳጥኖች ከአየር ማረፊያው በሰንደቅ አላማ ተሸፍነው ሲሸኙ በሺህ የሚቆጠር ህዝብ ተገኝቶ ነበር፡፡
2. አየር መንገዱ ለሟች ቤተሰቦች አደጋው ከደረሰበት ቦታ ላይ የተዘገነ አንድ ኪሎ አፈር እንደሰጠም የዜና ምንጩ ዘግቧል፡፡
3. ቢቢሲ እንደዘገበው ደግሞ የሟች ቤተሰቦች በአዲስ አበባ ወይም በማንኛውም አገር በሚገኝ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሽያጭ ቢሮ በመገኘት የዲኤንኤ ሳምፕል መስጠት እንደሚችሉ አስታውቋል፡፡
4. ኬንያ በአውሮፕላን አደጋው የሞቱብኝ ዜጎቼ ቁጥር 36 ነው አለች፡፡ ከዚህ ቀደም የሞቱት 32 እንደነበሩ የተገለፀ ሲሆን በኢትዮጵያ ምክትል የኬንያ አምባሳደር የሆኑት ጆርጅ ኦሪና ግን ዛሬ በሰጡት መግለጫ ‹‹አራቱ ዜጎቻችን የተጓዙት በሌላ አገር ፓስፖርት ስለሆነ ነው›› ብለው ቁጥሩ እንዲስተካከል ጠይቀዋል፡፡
5. ዴይሊ ኔሽን የተሰኘው የኬንያ ጋዜጣ በዛሬ እትሙ የሟች ቤተሰቦች እያንዳንዳቸው የ170 ሺህ ዶላር ካሳ እንደሚሰጣቸው ዘግቧል፡፡ በሞንትሪያል ኮንቬንሽን መሰረት አንድ ሰው በአውሮፕላን በረራ ላይ እያለ ለህልፈት ከተዳረገም ሆነ ጉዳት ከደረሰበት የሚሰጠው ካሳ መነሻ የ170 ሺህ ዶላር መሆኑንም ጋዜጣው አስታውቋል፡፡

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 5 years ago on March 17, 2019
  • By:
  • Last Modified: March 17, 2019 @ 9:48 am
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar